Posts

የነፃ ገበያ ውድድሩ ወዴት?

በዳዊት ታዬ የዜጎችን የመኖርያ ቤት ችግር ለመቅረፍ መንግሥት ተግባራዊ ለማድረግ ያቀደው የጋራ መኖርያ ቤቶች ግንባታ አተገባበር ሲያወያይ መሰንበቱ ይታወቃል፡፡ ማወያየት ብቻ ሳይሆን ብዙ ውዥንብር መፍጠሩንም ከሁለት ሳምንታት በፊት በየቀበሌው ደጃፍ የተመለከትነው ግርግር ይመሰክራል፡፡ የ40/60 የመኖርያ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ተጠቃሚ ለመሆን የነበረው ጉጉት ከልክ በላይ መሆኑንም የምንረዳበት ነው፡፡ የ40/60 የቤቶች ፕሮጀክት አተገባበር አሁንም ድረስ ብዥታ እንደፈጠረ ነው፡፡ ከዛሬ ነገ ምዝገባው ይጀመራል እየተባለ አሁንም ድረስ እየተጠበቀ ቢሆንም ነገሩ በእንጥልጥል ላይ ቀርቷል፡፡ ምዝገባው ለምን አልተጀመረም? ለሚለው ጥያቄ በቂ መልስ አልተገኘም፡፡ ሌሎች ግልጽ ያልሆኑ ጉዳዮችም እስካሁን ጥርት ብለው አልተገለጹም፡፡ በ40/60 የመኖርያ ቤቶች ፕሮጀክት እየተስተዋለ ያለው ሽፍንፍን ያለ አካሄድ እንደተጠበቀ ሆኖ ፕሮጀክቱን መሬት ላይ ለማውረድ ቤት ፈላጊው እንዲያሟላ የሚጠበቅበት የ40 በመቶ የቅድሚያ ክፍያ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በኩል በሚካሄድ ቁጠባ ስለመሆኑ ግን ለሁሉም ግልጽ ነው፡፡ ዜጎችን የቤት ባለቤት ለማድረግ የግንባታ ወጪውን ከባንክ ጋር አስተሳስሮ ግንባታውን ለማከናወን መቻሉ የሚደገፍ ነው፡፡ እንዲህ ዓይነት አሠራር እስካሁንም መዘግየት አልነበረበትም፡፡ ሆኖም የጋራ መኖርያ ቤቶችን ለመገንባት ወይም አሁን እንደታሰበው በ40/60 የመኖርያ ቤቶች ግንባታ ከባንክ ጋር በማስተሳሰር የሚሠራውን ሥራ ለአንድ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብቻ መስጠቱ እንደ ትክክለኛ ዕርምጃ ሊወስድ ግን አይችልም፡፡ በሌሎች የአገሪቱ ክፍሎች ያሉትን የመኖርያ ቤት ፈላጊዎችን ትተን በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ ብቻ ወደ በሚሊዮን የሚገመቱ ዜጎች የራሳቸው

ሹመት ብቻ ሳይሆን ሽረትም እንጠብቃለን

Image
ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ለፓርላማ ያቀረቡትን ሹመት ፓርላማው አፅድቆታል፡፡ ተጨማሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮችም ተሹመዋል፡፡ እያንዳንዱ ሹመት በፓርቲ ውስጥ ተሳትፎን ያረጋገጠ፣ አመኔታ ያሳደረ፣ የሕዝብ ጥቅምና ክብርን ግምት ውስጥ ያስገባ፣ ሕገ መንግሥቱን መሠረት ያደረገ መሆኑን አደራ በማለት ልዩ ትኩረት ሰጥታችሁ አረጋግጡ፣ ወስኑ፣ ፈጽሙ፣ ከማለት በስተቀር ለምን ሾማችሁ አንልም፡፡ ተሿሚዎች ኃላፊነታቸውን በሚፈለገው ብቃት፣ ሥነ ምግባርና ፍጥነት ሲወጡ ለማየት እንጓጓለን እንጂ፡፡ ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም፣ በአጠቃላይ ለመንግሥት፣ መንግሥታዊ ሥልጣን ለያዘው ኢሕአዴግ አንድ ዓብይና ጠቃሚ እንዲሁም አስቸኳይ የሆነ የምናቀርበው ጥያቄ ግን አለን፡፡ ጥያቄያችንም ስለመሾም ስታስቡ ስለሚሻሩም ታስባላችሁ ወይ? የሚል ነው፡፡ በግልጽ ለማስቀመጥ ከተፈለገም ክፍት ቦታ ላይ መሾም ብቻ አይደለም ቁም ነገሩ፡፡ የተያዘ የሥልጣን ወንበር ካለና ወንበሩ ላይ የተቀመጠው ሹምም ብቁ ካልሆነ፣ ከሥልጣኑ በማንሳት የተሻለ መሾም አስፈላጊ መሆኑን አምናችሁ ለመንቀሳቀስ ዝግጁ ናችሁ ወይ? የሚል ነው፡፡ መሾም አለባቸው ከሚለው ጎን ለጎን መሻር አለባቸው የሚባሉ እንዳሉም መታመን አለበት፡፡ በአሁኑ ጊዜ በተለያዩ የኃላፊነትና የሥልጣን ወንበሮች ላይ ተቀምጠው ሥራቸውን በሕግ፣ በግልጽነት፣ በኃላፊነትና በተጠያቂነት መንፈስ መወጣት ያልቻሉ አሉ፡፡ በአቅም ማነስ፣  በሥነ ምግባር ጉድለትና በፖለቲካዊ አመለካከት ምክንያት፡፡ መንግሥትም ሆነ ኢሕአዴግ ይህንን ሁኔታ በድፍረትና በቆራጥነት አይተው የተሰጣቸውን ኃላፊነት በብቃት የማይወጡትን ከኃላፊነት ማንሳት አለባቸው እንላለን፡፡ ብቁዎችን ሾሜያለሁ ከማለት ጎን ለጎን ብቃት የሌላቸውን ሽሬያለሁ ወይም እ

የጠቅላይ ሚኒስትሩ አዲሱ የካቢኔ አደረጃጀት እያነጋገረ ነው

Image
-    ካቢኔው በሕገ መንግሥቱ መሠረት አንድ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ይኖረዋል -    የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ ያላቸው ሁለት ባለሥልጣናት ተሹመዋል -    አዲሱ አደረጃጀት ከሌሎች ሕጐች ጋር ተቃርኖ አለው እየተባለ ነው በዮሐንስ አንበርብር የሥራ አስፈጻሚውን ከፍተኛ ሥልጣን በማግኘት አገሪቱን መምራት ከጀመሩ ሁለት ወራት ከቀናት ያስቆጠሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ሰሞኑን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በመቅረብ ካቢኔያቸውን በአዲስ መልክ እንዳደራጁ አስታውቀዋል፡፡ በዚህም መሠረት የሁለት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮችንና የሌሎች ሚኒስትሮችን ሹመት አፀድቀዋል፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትሩ አዲሱ የካቢኔ አደረጃጀትም መነጋገሪያ ሆኗል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚመሩት የሚኒስትሮች ምክር ቤት (ካቢኔ) በሕገ መንግሥቱና በመመሥረቻ አዋጁ የተጣለበትን ኃላፊነቶች በብቃት ለመወጣትና የአስፈጻሚነት ሚናውን በአግባቡ እንዲወጣ ለማድረግ፣ እንደ አዲስ በሦስት ዘርፎች መዋቀሩ አስፈላጊ መሆኑን ለፓርላማው አስታውቀዋል፡፡ በዚህም መሠረት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የዲፕሎማሲ፣ የደኅንነት፣ የመከላከያ እንዲሁም ከፍተኛና ግዙፍ (ሜጋ) ፕሮጀክቶችን በቀጥታ እንዲከታተሉ ተደርጓል፡፡ ከዚህ ውጪ ያሉ አስፈጻሚው የሚከታተላቸውን ተግባራት በብቃት ለመምራት የሚኒስትሮች ምክር ቤት በሦስት ዘርፎች እንዲዋቀር መደረጉን ገልጸዋል፡፡ ማኅበራዊ ጉዳዮችን፣ መልካም አስተዳደርና ረፎርምን፣ ፋይናንስና ኢኮኖሚን የሚመለከቱ ሦስት የሥራ ዘርፎች በአዲሱ የካቢኔ መዋቅር የተፈጠሩ ሲሆን፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የትምህርት ሚኒስትሩ ደመቀ መኮንን የማኅበራዊ ዘርፉን የሚመሩ መሆኑ ታውቋል፡፡ ከዚህ ቀደም የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤትና የካቢኔ ጉዳዮች ቢሮን በሚኒስት

ሲዳማ በዚህ ሳምንት የሬዲዮ ፕሮግራም በሲኣን 4 መደበኛ ጉባኤ ላይ ሰፊ ዘጋባ ይዞል

Image
The Nomonanoto Show

ተቃዋሚ ፓርቲዎች ሹመቱ ህገመንግስቱን የሚጋፋ ነው አሉ

Written by  መታሰቢያ ካሳዬ ኃላፊነቴን ከህዝቡ ጋር በአግባቡ እወጣለሁ - ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ሹመቱ ኢህአዴግ ያለበትን የፖለቲካ ሽኩቻ ለማስታገስ ያደረገው ነው የተሰጠው ሹመት በብቃት ላይ የተመሰረተ አይደለም ሹመቱ የቀድሞ ጠቅላይ ሚ/ር አሻራ አለበት (ተቃዋሚዎች) የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከትናንት በስቲያ ያፀደቀውን የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርነት፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት፣ የንግድ ሚኒስትርነት፣ የጤና ጥበቃ ሚኒስትርነትና ሌሎች ሹመቶችን አስመልክቶ ሹመቱ በአግባቡና በሥርዓት ያልተሰጠና ህጋዊ ሥርዓት የሚጐድለው ነው ሲሉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ተናገሩ፡፡ ሹመቱ ህገመንግስቱን የሚጋፋና ከህግና ሥርዓት ውጪ የተሰጠ ነው ሲሉም ተችተውታል፡፡ በአንድ ድምፀ ተአቅቦና በሙሉ ድምጽ ድጋፍ በፀደቀው ሹመት መሠረት ሁለት ተጨማሪ ጠቅላይ ሚኒስትሮችም ተሹመዋል፡፡ ከትናንት በስቲያ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተከናወነው ሥነሥርዓት ሹመታቸው የፀደቀላቸው አቶ ሙክታር ከድር በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የመልካም አስተዳደር እና ሪፎርም ክላስተር አስተባባሪና የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር ሚኒስትር፣ ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል በምክትል ጠቅላይ ሚ/ር ማዕረግ የፋይናንስና ኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪና የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር፣ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር፣ አቶ ታደለ ጫኔ የንግድ ሚኒስቴር ሚኒስትር እና ዶ/ር ከስተብርሃን አድማሱ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል፡፡ ብቸኛው የመድረክ ተወካይና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ግርማ ሰይፉ በሹመቱ ወቅት ድምፀ ተአቅቦ አድርገዋል፡፡ አቶ ግርማ ድምፀ ተአቅቦ ያደረጉበትን ምክንያት ሲናገሩም፤ ሹመቱ ከመሰጠቱ በፊት ስለተሿሚዎቹ ለም