Posts

‹‹የዳኝነት ሥርዓቱ ራሱን ከመቆጠብ መውጣት ይኖርበታል››

Image
አቶ ጌታሁን ካሣ፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሰብዓዊ መብት ማዕከል መምህር አቶ ጌታሁን ካሣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሰብዓዊ መብት ማዕከል መምህር ናቸው፡፡ የትግራይ ብሔራዊ ክልል የፍትሕ ቢሮ ኃላፊ፣ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ፣ እንዲሁም የሕገ መንግሥት አጣሪ ጉባዔ አባል በመሆንም ለሁለት የሥራ ዘመኖች አገልግለዋል፡፡ በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ትምህርት ቤትም በመምህርነት ሠርተዋል፡፡ በሕግ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ የሁለተኛ ዲግሪያቸውን ደግሞ ከእንግሊዝ ኩዊንስ ዩኒቨርሲቲ ያገኙ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሰብዓዊ መብት ማዕከል በሰብዓዊ መብት ዙሪያ የፒኤችዲ ምርምራቸውን በመሥራት ላይ ይገኛሉ፡፡  ሰለሞን ጎሹ  በዳኝነት ነፃነትና በሕገ መንግሥታዊ ትርጉም ላይ አነጋግሯቸዋል፡፡ ሪፖርተር፡- በኢትዮጵያ የፍትሕ አስተዳደር ውስጥ ዳኞች ምን ዓይነት ሚና ነው ያላቸው? አቶ ጌታሁን ፡- ከ1948 ዓ.ም ጀምሮ ያሉትን ሕገ መንግሥቶች ወይም ከዚያ በፊት የነበሩትን ሁኔታዎች ስንመለከት የዳኝነት ተቋማት ሥራ በዋነኛነት በሚነሱ ጉዳዮች ላይ የሁለት ወገኖችን ክርክርና ማስረጃ በመመልከትና በማገናዘብ ውሳኔ መስጠት ነው፡፡ የመንግሥት አደረጃጀትን በዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ውስጥ በሥልጣን ክፍፍል መርህ ስናይ ግን በሦስት እንከፍላለን፡፡ ሕግ አውጪው፣ ሕግ ተርጓሚውና ሕግ አስፈጻሚው ይኖራሉ፡፡ በአገራችንም እነዚህ የመንግሥት አካላት አሉን፡፡ አንዱ በአንድ ወቅት ከነበረው የሚለይበት ሁኔታ ይኖራል፡፡ የተለያዩ ገጽታዎችም አሏቸው፡፡ ለምሳሌ የተጻፈ ሕገ መንግሥት ከኖረን ጊዜ ጀምሮ ያለውን ብንመለከት የዳኝነትና የሕግ አስፈጻሚነት ሥልጣን በአንድ አካባቢ ተደራርቦ የምናገኝበት ሁኔታ ነበር፡፡ አሁን ባለው

የመጀመሪያው ''ሲዳማ በዚህ ሳምንት'' የኢንተርኔት ላይ የሬዲዮ ፕሮግራም ኣየር ላይ ውሏል

Image
የሬዲዮ ፕሮግራሙ በዚህ ሳምንት ዝግጅቱ በተለያዩ የኣለማችን ክፍሎች የሚገኙትን የሲዳማ ዳይስፖራ የሁለተኛ ድግሪ ተማሪዎችን ኣሳትፏል። እንደኣዘጋጆቹ ከሆነ ከኢትዮጵያ ውጭ እና ሲዳማ የሚገኙ  የሬድዮ ፕሮግራሙን የምከተታዮች በዝግጅቱ ላይ ኣስተያየት እንዲስጡ እና በፕሮግራሙ ላይ በመሳተፊ ልምዳቸውን እንዲያካፍሉ ጥሪ ኣቅርበዋል። የ''ሲዳማ በዚህ ሳምንት የሬድዮ ፕሮግራም'' ኣዘጋጅን በምከተለው ኣድራሻ ማግኘት ይቻላል ፦ e-mail: nomonanoto@gmail.com   ሲዳማ ሻው ለማድመጥ እዚህ ላይ ይጫኑ

«ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፉ የምርጫና ዴሞክራሲ አማካሪ ተቋም ጋር ተባብሮ ለመሥራት ዝግጁ ናት» ጠ/ሚ ኃይለማርያም

Image
ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፉ የምርጫና ዴሞክራሲ አማካሪ ተቋም ጋር ተብብሮ ለመሥራት ዝግጁ መሆኗን ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ አረጋገጡ። ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም የአማካሪ ተቋሙን ዋና ጸሐፊ ቪዳር ሄልግሰን ጥቅምት 22/2005 በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው ሲያነጋግሩ እንደገለፁት ኢትዮጵያ ከተቋሙ ጋር ተባብራ ለመሥራት ፍላጎቷ ነው። ተቋሙ በኢትዮጵያ በ2002 የተካሄደውን ብሔራዊና ክልላዊ ምርጫ በምርምር ያቀረበው የሥነ ምግባር መመሪያ በሁሉም ወገኖች ዘንድ ተቀባይነት ያተረፈ እንደነበር አስታውሰዋል። መንግሥት ቀደም ሲል የተፈጠረውን ግንኙነት መሠረት በማድረግ ከተቋሙ ጋር በቀጣዩም ተባብሮ ለመሥራት ፍላጎት እንዳለውም አስታውቀዋል፡፡ ተቋሙ በምርጫና በዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ላይ አዳዲስ ሐሳቦችን በማመንጨት እንዲያቀርብም መጠየቃቸውን አንድ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣን ለጋዜጠኞች ገልፀዋል። ሚስተር ሄልገሰን በበኩላቸው በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሞት ጥልቅ ኀዘን እንደተሰማቸው አስታውቀው፣ በእሳቸው አመራር ዘመን በኢትዮጵያ የተጀመሩ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ወደፊትም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም እምነታቸውን ገልፀዋል፡፡ በተለይ በአገሪቱ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማት እስካሁን የተመዘገቡ ስኬቶች በአዲሱ አመራር ለማስቀጠል በስፋት ተነጋግረዋል፡፡ ዋና ፀሐፊው በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ የኢኮኖሚ ኮሚሽንና በአፍሪካ ኅብረት ትብብር አዲስ አበባ ውስጥ ''ወጣቶችና የአፍሪካ ዴሞክራሲ'' በሚል ርዕስ በተዘጋጀ ዐውደ ጥናት እየተሳተፉ ናቸው። http://www.ertagov.com/amerta/erta-news-archive/49-erta-tv-hot-news-ad

ጠ/ሚኒስትሩ ከ “ልማታዊ ተቃዋሚዎች” ጋር ቢወያዩስ?

Written by  - ኤልያስ - ጋዜጠኞች ለኢትዮጵያ ህዳሴ አያስፈልጉም እንዴ? አባት ተርብ የሆኑ ነጋዴ ናቸው፡፡ ሴት ልጃቸው ደግሞ ሰቃይ ተማሪ ናት - በአሜሪካ ዩኒቨርስቲ፡፡ በነገራችን ላይ ሁለቱም አሜሪካውያን ሲሆኑ የሚኖሩትም እዚያው አሜሪካ ነው፡፡ አባት ባለሃብቶች ላይ ከፍተኛ ግብር የሚጥለውን የዲሞክራት ፓርቲ አይደግፉም፡፡ የሪፐብሊካኖች ቀንደኛ ደጋፊ ናቸው፡፡ ልጅት ደግሞ ዲሞክራት ናት፡፡ የኮሌጅ ፕሮፌሰሯም እንዲሁ፡፡ እናም ሁሌ ይወያያሉ - የአሜሪካን ሃብት ጠቅልለው ስለያዙት 1በመቶ ባለሃብት አሜሪካውያንና 99 በመቶ ምስኪኖች፡፡ “እነዚህ ስግብግቦች እኮ ናቸው …” እያሉ ያማሉ፤ ይተቻሉ፡፡ (ኢህአዴግ ኪራይ ሰብሳቢ ባለሃብት እንደሚለው) አንድ ቀን ልጅትና አባት ቁጭ ብለው ሲያወጉ የተለመደው አከራካሪው ጉዳይ ተነሳ፡፡ “መንግስት የጣለብህን ግብር እየከፈልክ እኮ አይደለም …ህዝብ እየበዘበዝክ ነው… በጣም ኢ-ሰብዓዊ ተግባር ነው” ስትል ልጅ አባቷን ትወቅሳለች፡፡ አባት ከመናደድ ይልቅ መላ አመጡ፡፡ “ግን ትምህርት እንዴት ነው የእኔ ልጅ? ውጤትስ?” ይሏታል “እኔስ ቀንቶኛል … 4A እና 3B አግኝቻለሁ … ጓደኛዬ ግን ጠቅላላ C ነው ያመጣችው” “ታዲያ ካንቺ 4Aዎች አታካፍያትም?” ጠየቁ አባት (ለብልሃታቸው) “እንዴ … ለፍቼ እኮ ነው ያገኘሁት” አባት ፈገግ ብለው “እኔም ለፍቼ ያመጣሁትን እኮ ነው ስጥ የምትይኝ… ገባሽ?” አሏት፡፡ (የገባት ግን አይመስለኝም) እኔ የምለው የአሜሪካን ምርጫ እየተከታተላችሁ ነው? እኔማ ቀናሁባቸው! በነገራችሁ ላይ ኢቴቪ የኦባማ (ዲሞክራቶች) ደጋፊ ነው እንዴ? (ጥያቄ ነው!) የሰሞኑን የአሜሪካ ምርጫ ዘገባዎች በኢቴቪ ካስተዋላችሁ እኮ የአሜሪካ ዲሞክራት ፓርቲ ደጋፊ ነው የሚመስላችሁ፡፡ ኢቴቪ ዲሞክራቶችን

ዓለም አቀፍ የቡና ጉባዔ ይካሄዳል

አዲስ አበባ፡- የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ ቡና ጉባዔ በአዲስ አበባ ለሁለት ቀናት እንደሚካሄድ ኢትዮጵያን ኮፊ ኤክስፖርተስ አሶሴሽን አስታወቀ። አሶሴሽኑ ለዝግጅት ክፍላችን በላከው መግለጫ እንዳመለከተው፤ «የቡናችን መገኛ ታሪካችንን ማጠናከር» በሚል መሪ ሃሳብ ጥቅምት 29 እና 30 ቀን 2005 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሒልተን ሆቴል በሚካሄደው በዚህ ጉባዔ ከ250 በላይ ተሣታፊዎች ይገኛሉ። ከንግድ ሚኒስቴርና ሌሎች አጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር የሚካሄደው የዚህ ጉባዔ ዓላማ የኢትዮጵያ ቡና በዓለም አቀፍ ገበያ ውስጥ የሚኖረውን ድርሻ ማሳደግ በሚያስችሉ ስልቶች ላይ ለመወያየትና መረጃና ልምድ ለመለዋወጥ ነው። ባለድርሻ አካላት በቡና ዓለም አቀፍ ግብይት ላይ ስላሉት ዕድሎችና ተግዳሮት በቂ ግንዛቤ እንዲያገኙ እና የኢትዮጵያን ቡና ልዩ ጣዕም በማስተዋወቅ ረገድ መጫወቱ ስለሚገባቸው ሚና እንዲያውቁ ለማድረግ ታስቦ መዘጋጀቱንም መግለጫው አመልክ ቷል። በጉባዔ በቡና ንግድ ዘርፍ ላይ ዋነኛ ተዋንያን የሆኑትን ላኪዎች፣ አቅራቢዎች፣ ወኪሎች፣ ማኅበራት፣ የክልል ግብርና ቢሮዎች፣ የንግድ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ፣ የግብርና ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ባለሥልጣን፣ የአካባቢ የፋይና ንስ ተቋማት፣ ዓለም አቀፍ ቡና ገዥ ኩባንያዎች ይሣተፋሉ። የዓለም አቀፉ የቡና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ሚስተር ሮቤይሮ ኦሊቬይራ ሲልቫ፣ የአውሮፓ ሕብረት ልዑክ መሪ እና በኢትዮጵያ የዩኤስ ኤይድ ዳይሬክተር በጉባዔው ላይ ተገኝተው ንግግር ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል። «ወደ ውጭ የሚላከው ቡና በ25 በመቶ የሚጨምር፣ መጠኑም ከ200ሺ ቶን በላይ፣ የሚገኘው የውጭ ምንዛሬ አንድ ቢሊዮን ዶላር እንደሚልቅ ይጠበቃል» ሲል መግለጫው አመልክቷል።