የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለማቃለል አገራዊ የህዝብ ንቅናቄ ይካሄዳል
አዲስ አበባ፡-በየሥራ መስኩ የሚታዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለማቃለል የሚያስችል ሕዝባዊና አገራዊ ንቅናቄ በተያዘው ዓመት እንደሚካሄድ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ አስታወቁ። የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ ትናንት የሕዝብ ተወካዮች እና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች የአራተኛ ዙር የሥራ ዘመን ሦስተኛ ዓመት የጋራ ስብሰባ በከፈቱበት ወቅት እንደተናገሩት፤ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለማስወገድና የተገኙ ስኬቶችን ለማስጠበቅ የሚያስችል አገራዊ እንቅስቃሴ በዚህ ዓመት ይካሄዳል። በአገር አቀፍ ደረጃ በሚካሄደው መልካም አስተዳደርን የማጐልበት ሕዝባዊ ንቅናቄ የሚመለከታቸው አካላት የበኩላቸ ውን ሚና እንዲጫወቱ ጥሪ አቅርበዋል። ሕዝባዊና አገራዊ ንቅናቄው በአሁኑ ወቅት በተጨባጭ የሚታዩ ችግሮችን ነቅሶ በማውጣት የመፍታትና የሕዝብን እርካታ የማረጋገጥ ግብ ያለው መሆኑን ፕሬዚዳንቱ አመልክተው፤ ለዚህ ግብ መሳካት ሁሉም ሕዝብ በንቃትና በተደጋጋፊነት እንዲሣተፍና የመልካም አስተዳደር ራዕዩን እውንነት እንዲረጋገጥ የዘርፉ ተዋናዮች ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። እንደ ፕሬዚዳንቱ ገለፃ፤ ላለፉት 21 ዓመታት በሀገሪቱ ዴሞክራሲያዊና መልካም አስተዳደር የሰፈነበት ሥርዓት ለመገንባት በተደረገው ጥረት የዜጎችና የሕዝቦችን ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ለማስከበር ሰፊ እንቅስቃሴ ተደርጓል። ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶችን በፅናት ከማክበር ጀምሮ በነፃ የሕዝብ ምርጫ መንግሥትን እስከመመሥረት ድረስ በርካታ መሠረታዊ የዴሞክራሲያዊ ለውጥ ተግባራት ተከናውነዋል። ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶችን ለማስጠበቅና ለማጠናከር ሲባል የተቋቋሙት በየደረጃው ያሉት ምክር ቤቶች፣ የሕግ ተርጓሚና የአስፈፃሚው አካላት በሀገሪቱ የግልፅነትና የተጠያቂነት ሥር