መረጃ:- የግልጽነትና የተጠያቂነት ቁልፍ መሳሪያ
ከኢፌዲሪ ህገ- መንግስት አምስት መሰረታዊ መርሆዎች ውስጥ የመንግስት አሰራርና ተጠያቂነት አንዱ ነው፡፡ የግልጽነትና የተጠያቂነት መርህ በመንግስት ሀላፊዎች የሚወሰዱ ውሳኔዎችና የስራ እቅስቃሴዎች ለህዝቡ ግልጽ መሆናቸውንና ህዝቡም ይህንን በተመለከተ ያሉትን መረጃዎች ለማግኘት ያለውን መብት የሚያረጋግጥ መርህ ነው፡፡ የግልጽነትና የተጠያቂነት መርህ የዲሞክራሲ ዋልታ በመሆኑም ከመርሁ ተግባራዊነት ውጪ ዲሞክራሲን ማስፈን የማይታሰብ ነው፡፡ ለዲሞክራሲያዊ ስርዓት መጎልበት ትልቁን ድርሻ የሚይዘውን የህዝቦች ተሳትፎና የስልጣን ባለቤትነት ለማረጋገጥም ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት የመንግስት አሰራርን እውን ማድረግ የግድ ይላል፡፡ ዜጎች በፖለቲካና በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግና የመንግስት ሀላፊዎች ሀላፊነታቸውን በአግባቡ እየተወጡ መሆኑን ለመመርመር ተገቢውን መረጃ ሊያገኙ ይገባል፡፡ ግልጽነትም ትክክለኛና ወቅታዊ መረጃን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ማድረግ ሲሆን ለተጠያቂነትም እንደ ቅድመ ሁኔታ ይቀመጣል፡፡ በመሆኑም የግልጽነትና የተጠያቂነት መርህ የህዝቦችን ተሳትፎ ከማሳደጉም በላይ የዜጎችን መረጃ የማግኘት መብት የሚያረጋግጥ ነው፡፡ ዜጎች መረጃ የመጠየቅ፣ የማግኘትና የማስተላለፍ መብታቸው መከበሩ አንድም ተሳትፎአቸውን ለማሳደግ ሌላም የግልጽነትና የተጠያቂነት መርህን በመተግበር የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ተግባራዊነትን ለማረጋገጥ የሚኖረው ድርሻ የጎላ ነው፡፡፡ ዜጎች መረጃ ለማግኘት በራሳቸው ከሚያደርጉት እንቅስቃሴ በተጨማሪም ጠቃሚ የሆኑ መረጃዎችን በመፈለግና ለህዝቡ ተደራሽ በማድረግም የመገናኛ ብዙሀን ጉልህ ሚና አላቸው፡፡ የመገናኛ ብዙሀንና የመረጃ ነጻነት አዋጅ ቁጥር 590/2000 የመደንገጉ ምክንያትም የዜጎችን መረጃ የማግኘት መብትንና የመገ