አቶ ኃይለማርያም፤ “ሜዳውም ፈረሱም ያው…” ታድያ በቅጡ ይጋልቡ!
አቤ ቶኪቻው ኃይለማርያም ደሳለኝ በጠቅላይ ሚኒስቴሩ ወንበር ላይ ለመቀመጥ ቤተመንግስቱ በራፍ ላይ ቆመዋል። ለነገሩ እንኳ ሰውየው ደጃፍ ላይ ከቆሙ ቆይተዋል። ነገር ግን የኢህአዴግ ሰዎች “አናስገባም ሰርገኛ እደጅ ይቆይ…” ብለው ደጅ ሲያስጠኗቸው ሰነባበቱ። ይገበሉ ተብሎ ሲጠበቅ የነበረው ቢያንስ ኢቲቪ እና የመንግስት “ባሉካዎች” የጠቅላይ ሚኒስሩን ሞት በሰሙ በሁለት እና ሶስት ቀናት ውስጥ ነበር። ነገር ግን ይኸው ዛሬም ገና ፓርላማው ጠቅላይነታቸውን እስኪያፀድቅላቸው እንደ ቆሎ ተማሪ ደጅ መቆም ግዴታቸው ሆኗል። አቶ ሀይለማሪያም የኢህአዴግ ሊቀመንበርነትን ስልጣን ከያዙ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ “ሲሲቲቪ” ለተበለ ቴሌቪዥን ጣቢያ በሰጡት ቃል “የእኔ አመራር የጋራ አመራር መርህን የተከተለ ነው” ካሉ በኋላ፤ “እንደሚታወቀው የመለስም አመራር ለግለሰብ የበላይነት ቦታ የማይሰጥ የቡድን ስራ የጎላበት አመራር ነበር” ብለው የማናውቀውን ነገር ነግረውናል። እውነቱን ለመናገር እኛ የምናውቀው አቶ መለስ “ሁሉን ቻይ” የነበሩና ሁልገዜም ብቻቸውን እንጂ በጋራ ሲሰሩ አላየንም። እርግጥ ደንብ ነውና ሙትን ሲያነሱ ደግ ደጉን ነው። ስለዚህ ስለ መለስ የሚያወሩት በሙሉ ፅቡቅ ፅቡቁን ቢሆን ግድ የለም… መምህር ኃይለማሪያም ሆይ መለስን ለአሁኑ እንተዋቸው እና በእርስዎ ጉዳይ እናውጋ… እናልዎ… አሁን ሜዳው ሜዳውም ፈረሱም በእጅዎ ነው። እንግዲህ በቅጡ መጋለብ የእርስዎ ፈንታ ነው። መምህር ሆይ ይቅርታ አንድ ጊዜ ወደ መለስ መለስ እንበልና አንድ ነገር ሹክ ልበልዎትማ ባለፈው ጊዜ የመለስ ለቅሶ ላይ ጥቁር በጥቁር ለብሶ “እንባ የተራጨው” ህዝቡ ሁላ ከኢህአዴግ ጎን ነው ስለዚህ እንዳሻኝ እሆናለሁ ብለው እንዳይሸወዱ… ልብ ያድርጉልኝ “እንባ የተራጨው” የምትለዋ ቃል ራሱ