Posts

ሀገሪቱን አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትርና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጋራ ይመሯታል ተባለ

Image
New ኢሳት ዜና:-በመስከረም ወር 2005 ዓ.ም የኢህአዴግ ምክር ቤት በአቶ መለስ ዜናዊ ምትክ በሚያካሂደው ምርጫ የሚመረጠው ሊቀመንበር እና ምክትል ሊቀመንበር ድርጅቱን ለስድስት ወራት ብቻ በጋራ እንደሚመሩ አቶ ሬድዋን ሁሴን የግንባሩ ጽ/ቤት ኃላፊ አስታወቁ፡፡ አቶ ሬድዋን ዛሬ ከወጣው አዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ የግንባሩ መተዳደሪያ ደንብ ቀጣዩ ጉባዔ ከሁለት እስከ ሁለት ዓመት ተኩል ባለው ጊዜ ውስጥ ይካሄዳል በሚለው መሰረት ቀጣዩ ጉባዔ ከስድስት ወራት በኃላ እንደሚካሄድ ጠቁመው እስከዚያ ከአራቱም አባል ድርጅቶች 45 ሰዎች በድምሩ 180 አባላት የተወከሉበት የግንባሩ ም/ቤት በተጓደሉት አባላት ምትክ ግንባሩን “በጋራ የሚመሩ” ሊቀመንበር እና ምክትል ሊቀመንበር ይመርጣል ብለዋል፡፡ “ከስድስት ወራት በኃላ የግንባሩ ጉባዔ ሲካሄድ ሊቀመንበሩና ምክትል ሊቀመንበሩ ብቻ ሳይሆን የሥራ አስፈጻሚና የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላትም ሥልጣናቸውን ያስረክባሉ፡፡ከማንኛውም አባል ጋር ወርዶና የጉባዔው አባል ሆኖ ከተመረጠ ይመረጣል፡፡እስከዚያው ግን የሊቀመንበርነት ቦታ ተጓድሎአል፡፡ተጓደለውን ቦታ የሚመርጠው ጉባዔው ሳይሆን ምክርቤቱ በመሆኑ በዚሁ መሰረት በመስከረም ወር ይመርጣል፡፡ቀጣይ ስድስት ወር ሲሞላ አዲሱ ሊቀመንበር ሌላ የጉባዔ አባላት ይሆኑና እንደገና ምርጫ ተደርጎ የሚመረጡ ከሆነ ይመረጣሉ” ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ሰሞኑን  የኢህአዴግ ሥራ አስፈጻሚ የሰሞኑ ጉባዔ ስላሳለፈው ውሳኔ ተጠይቀው በሰጡት ምላሸ “…የሁልጊዜም የድርጅቱ መሰረታዊ እምነት ሕዝቡን ወደተሻለ ደረጃ በመውሰድ ላይ ያነጣጠረ ፣የህዝቡን ሕይወት በመቀየር ላይ ያነጣጠረ፣የሕዝቡን ሕይወት በመቀየር መሰረታዊ የሆነውን ለውጥ በሃገሪቱ ለማምጣት መሰዋዕትነት መክፈል ላይ ያተኮረ ነው፡፡በመሆኑም

የአመት በዓል ገበያ ለብዙሀኑ ኢትዮጵያውያን የማይቀመስ ሆኖል

ጳጉሜን ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በአዲስ አመት ዋዜማ አዲስ አበባ የፍርሃትና  የዝምታ ድባብ ሰፍሮባታል:: የአመት በዓል ገበያም ለብዙሀኑ ኢትዮጵያውያን የማይቀመስ ሆኖል:: በመርካቶና  በአዲሱ ገበያ አካባቢ ዘጋቢያችን ተዘዋውሮ  እንደተመለከተው 50 ኪሎ ማኛ ጤፍ 1200 ብር ኩንታሉ 2400 ብር ጠቆር ያለው ጤፍና ሰርገኛ እንደ ደረጃው ከ1400 ብር እስከ  1800 ብር የኤልፎራ ዶሮ ብር 100 እየተሸጠ ሲሆን የሀበሻ  ዶሮ  በገበያ ላይ እንደ ኪሎው  ከመቶ ሀምሳ  እስከ  210 እየተሸጠ ነው:: አንድ  እንቁላል 2 ብር ከ50 ሳንቲም ሲሆን በግ ከ1300 እስከ  3500 ብር ነገር ግን በመርካቶ አካባቢ ግን ከዚህ ወደድ እንደሚል ዘጋቢያችን ገልፆልናል::  ቅቤ ከብር 150 እስከ 160 ሲሸጥ የሸኖ ለጋ ቅቤ ግን እስከ 200 ብር በመሸጥ ላይ ነው:: በሬ ከ15000 እስከ 20000 እየተሸጥ ነው::

Year of Incongruence

Change is the one theme that I admire devotedly. I often think that the root cause of many of the societal problems that I observe in our society is resistance to change. A person ready to change is a person with a confidence to leap forward in life, I even argue. It was with the sole objective of experiencing change that I get involved in an industry far from my career objective, business advisory. What I have identified in my over one year stay in the media industry is, however, that it is an environment of information but not knowledge, hard work but less recognition, overwork but meagre income, and visibility but not upward mobility. In thinking about the just-ended year, I came across many occasions that I worked hard to break myself. These were times that I had the most satisfaction out of life. Yet, they were all useless for they were accompanied by little more than a good feeling. For a boy who has grown in a family wherein outstanding works are awarded with jovial rec

ኢህአዴግ በአዲሱ ዓመት ያሞላቅቀን!

“የፓርቲዬ ባህል አይፈቅድልኝም” የሚል ሰበብ አንቀበልም! በሀዘን ክፉኛ የጨፈገገንን ደባሪ ዓመት ዛሬ እንሸኘዋለን - እንዲህ ያለ ዓመት ተመልሶ እንዳይመጣ እየተመኘን (ኧረ ፀሎትና ምህላም ያስፈልገዋል!) ግን በ2004 ምን መዓት ነው የወረደው? ብቻ በዚሁ በቃችሁ ይበለን! አሁን ወደ ዕለቱ ወጋችን ልመልሳችሁ፡፡በዛሬዋ የአዲስ ዓመት ዋዜማ ላይ ሆኜ ምን እንዳማረኝ ታውቃላችሁ? በቃ … መሞላቀቅ፡፡ ግን ደግሞ በወላጅ ወይም በአያት አሊያም በፍቅረኛ አይደለም፡፡ እኔ መሞላቀቅ ያማረኝ በገዢው ፓርቲ ነው፡፡ (አሞላቆን ስለማያውቅ ይሆን?) በርግጥ ይሄ ጥያቄ የእኔ ብቻ አይደለም - የህዝብ ነው፡፡ ማስረጃ ካስፈለገም ፒቲሽን አሰባስቤአለሁ፡፡ እናም ኢህአዴግ እስኪበቃን ድረስ እንዲያሞላቅቀን እፈልጋለሁ፡፡ እየቀለድኩ እንዳይመስላችሁ… ከምሬ ነው፡፡ በቃ በአዲሱ ዓመት ሙልቅቅ ማለት አምሮኛል፡፡ እንደ ቦሌ ልጆች! እኔ የምለው… ኢህአዴግ እኛን ማሞላቀቅ ያቅተዋል እንዴ? ኧረ አያቅተውም፡፡ ዋናው ነገር የልብ መሻት ነው (When there is a will, there is a way እንዲል ፈረንጅ) መቼም አውራ ፓርቲያችን ሰበብ አያጣምና “የፓርቲያችን ባህል፤ ማሞላቀቅ አይፈቅድም” ሊለኝ ይችላል (አልሰማሁም እለዋለኋ!) እርግጥ በኢህአዴግ መዝገበ ቃላት ውስጥ “መሞላቀቅ” የሚል ቃል ላይኖር ይችላል፡፡ ግን ደግሞ የህዝብ ጥያቄ ነው እያልኩት ነው (የህዝብ አጋር ነኝ ይል የለ!) ለህዝብ ጥቅም ሲል ይቸገራ! (ለህዝብ ጥቅም እያለ ስንት ነገር ያደርጋል እኮ) ደሞ እኮ 21 ዓመት ሙሉ ለገዛው ህዝብ ከዚህም በላይ ቢያደርግ አይቆጭም (ገና 30 እና 40 ዓመት ሊገዛን ያስብ የለ!) ስለዚህ ሰበብ መደርደሩን ትቶ ጭክን ብሎ ያሞላቀን - በአዲሱ ዓመት! እንዴት ነው የሚያሞላ

2004 ኢትዮጵያ ታላላቅ ሰዎቿን ያጣችበት ዓመት

Image
ጊዜው በጣም ይነጉዳል፡፡ ትናንት የጀመርነው 2004 ዓ.ም ዛሬ ተጠናቋል፡፡ አንድ ዓመት እንደቀልድ እልም ይላል፡፡ መስከረም አልፎ መስከረም ሲተካ ሁሉም በየእምነቱ ለፈጣሪ እራሱን አደራ ይሰጣል፤ ‹‹ዓመት ከዓመት በሰላም አሸጋግረን›› ሲል፡፡ የተፈቀደላቸው ሲሻገሩ ያልተፈቀደላቸው ደግሞ ዓመቱን ሳይሻገሩ ይቀራሉ፡፡ ይህ የተፈጥሮ ዑደት ነው እና እንዲህ እያለ በያመቱ ይቀጥላል፡፡ ማንም ከሞት የሚቀር የለምና፡፡ ባጠናቀቅነው 2004 ዓ.ም ኢትዮጵያ ታላላቅ ሰዎቿን አጥታለች፡፡ ያሳለፍነው ዓመት ወጣት ጋዜጠኞችንም ወስዶብናል፡፡ በየሁለት ወሩ እና በየሦስት ወሩ አንዳንዴም በአንድ ወር ውስጥ የሁለት ታላቅ ሰዎች ሕይወት አልፏል፡፡ ገና በመስከረም ወር የተጀመረው ሐዘን እስከ ነሐሴ ዘልቋል፡፡ አንጋፋው ተርጓሚ፣ ጋዜጠኛና ደራሲ ማሞ ውድነህ እና አንጋፋው ደራሲ ስብሐት ገብረእግዚአብሔር በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ነበር ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት፡፡ ኢትዮጵያን ለ21 ዓመታት በጠቅላይ ሚኒስትርነት የመሩት መለስ ዜናዊ እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን ለ20 ዓመታት የመሩት አቡነ ጳውሎስም በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በጥቂት ቀናት ልዩነት ነው ሕይወታቸው ያለፈው፡፡ የእውቅና ታላላቅ ሰዎች ተከታትሎ ማለፍ የተነሳም ከዐይን የራቀ እና የታመመ ሰው ሁሉ ‹‹ሞተ›› እየተባለ ወሬ ሲናፈስበት የዘለቀ ዓመት ነበር- 2004 ዓ.ም፡፡ አርቲስት አስናቀች ወርቁ (1927-2004) በተጠናቀቀው የኢትዮጵያውያን 2004 ዓ.ም የመጀመሪያ ሣምንት ከግማሽ ምእት ዓመት በላይ በክራር ቅኝቷ የብዙዎችን ቀልብ ገዝታ የኖረችው አስናቀች ወርቁ ኅልፈተ ሕይወት የተሰማበት ወር ነበር፡፡ በቀድሞው ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቴአትር (በአሁኑ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር) በታላላ