Posts

ኢህአዴግ በአዲሱ ዓመት ያሞላቅቀን!

“የፓርቲዬ ባህል አይፈቅድልኝም” የሚል ሰበብ አንቀበልም! በሀዘን ክፉኛ የጨፈገገንን ደባሪ ዓመት ዛሬ እንሸኘዋለን - እንዲህ ያለ ዓመት ተመልሶ እንዳይመጣ እየተመኘን (ኧረ ፀሎትና ምህላም ያስፈልገዋል!) ግን በ2004 ምን መዓት ነው የወረደው? ብቻ በዚሁ በቃችሁ ይበለን! አሁን ወደ ዕለቱ ወጋችን ልመልሳችሁ፡፡በዛሬዋ የአዲስ ዓመት ዋዜማ ላይ ሆኜ ምን እንዳማረኝ ታውቃላችሁ? በቃ … መሞላቀቅ፡፡ ግን ደግሞ በወላጅ ወይም በአያት አሊያም በፍቅረኛ አይደለም፡፡ እኔ መሞላቀቅ ያማረኝ በገዢው ፓርቲ ነው፡፡ (አሞላቆን ስለማያውቅ ይሆን?) በርግጥ ይሄ ጥያቄ የእኔ ብቻ አይደለም - የህዝብ ነው፡፡ ማስረጃ ካስፈለገም ፒቲሽን አሰባስቤአለሁ፡፡ እናም ኢህአዴግ እስኪበቃን ድረስ እንዲያሞላቅቀን እፈልጋለሁ፡፡ እየቀለድኩ እንዳይመስላችሁ… ከምሬ ነው፡፡ በቃ በአዲሱ ዓመት ሙልቅቅ ማለት አምሮኛል፡፡ እንደ ቦሌ ልጆች! እኔ የምለው… ኢህአዴግ እኛን ማሞላቀቅ ያቅተዋል እንዴ? ኧረ አያቅተውም፡፡ ዋናው ነገር የልብ መሻት ነው (When there is a will, there is a way እንዲል ፈረንጅ) መቼም አውራ ፓርቲያችን ሰበብ አያጣምና “የፓርቲያችን ባህል፤ ማሞላቀቅ አይፈቅድም” ሊለኝ ይችላል (አልሰማሁም እለዋለኋ!) እርግጥ በኢህአዴግ መዝገበ ቃላት ውስጥ “መሞላቀቅ” የሚል ቃል ላይኖር ይችላል፡፡ ግን ደግሞ የህዝብ ጥያቄ ነው እያልኩት ነው (የህዝብ አጋር ነኝ ይል የለ!) ለህዝብ ጥቅም ሲል ይቸገራ! (ለህዝብ ጥቅም እያለ ስንት ነገር ያደርጋል እኮ) ደሞ እኮ 21 ዓመት ሙሉ ለገዛው ህዝብ ከዚህም በላይ ቢያደርግ አይቆጭም (ገና 30 እና 40 ዓመት ሊገዛን ያስብ የለ!) ስለዚህ ሰበብ መደርደሩን ትቶ ጭክን ብሎ ያሞላቀን - በአዲሱ ዓመት! እንዴት ነው የሚያሞላ

2004 ኢትዮጵያ ታላላቅ ሰዎቿን ያጣችበት ዓመት

Image
ጊዜው በጣም ይነጉዳል፡፡ ትናንት የጀመርነው 2004 ዓ.ም ዛሬ ተጠናቋል፡፡ አንድ ዓመት እንደቀልድ እልም ይላል፡፡ መስከረም አልፎ መስከረም ሲተካ ሁሉም በየእምነቱ ለፈጣሪ እራሱን አደራ ይሰጣል፤ ‹‹ዓመት ከዓመት በሰላም አሸጋግረን›› ሲል፡፡ የተፈቀደላቸው ሲሻገሩ ያልተፈቀደላቸው ደግሞ ዓመቱን ሳይሻገሩ ይቀራሉ፡፡ ይህ የተፈጥሮ ዑደት ነው እና እንዲህ እያለ በያመቱ ይቀጥላል፡፡ ማንም ከሞት የሚቀር የለምና፡፡ ባጠናቀቅነው 2004 ዓ.ም ኢትዮጵያ ታላላቅ ሰዎቿን አጥታለች፡፡ ያሳለፍነው ዓመት ወጣት ጋዜጠኞችንም ወስዶብናል፡፡ በየሁለት ወሩ እና በየሦስት ወሩ አንዳንዴም በአንድ ወር ውስጥ የሁለት ታላቅ ሰዎች ሕይወት አልፏል፡፡ ገና በመስከረም ወር የተጀመረው ሐዘን እስከ ነሐሴ ዘልቋል፡፡ አንጋፋው ተርጓሚ፣ ጋዜጠኛና ደራሲ ማሞ ውድነህ እና አንጋፋው ደራሲ ስብሐት ገብረእግዚአብሔር በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ነበር ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት፡፡ ኢትዮጵያን ለ21 ዓመታት በጠቅላይ ሚኒስትርነት የመሩት መለስ ዜናዊ እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን ለ20 ዓመታት የመሩት አቡነ ጳውሎስም በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በጥቂት ቀናት ልዩነት ነው ሕይወታቸው ያለፈው፡፡ የእውቅና ታላላቅ ሰዎች ተከታትሎ ማለፍ የተነሳም ከዐይን የራቀ እና የታመመ ሰው ሁሉ ‹‹ሞተ›› እየተባለ ወሬ ሲናፈስበት የዘለቀ ዓመት ነበር- 2004 ዓ.ም፡፡ አርቲስት አስናቀች ወርቁ (1927-2004) በተጠናቀቀው የኢትዮጵያውያን 2004 ዓ.ም የመጀመሪያ ሣምንት ከግማሽ ምእት ዓመት በላይ በክራር ቅኝቷ የብዙዎችን ቀልብ ገዝታ የኖረችው አስናቀች ወርቁ ኅልፈተ ሕይወት የተሰማበት ወር ነበር፡፡ በቀድሞው ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቴአትር (በአሁኑ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር) በታላላ

Dr. Marty Nathan: For mothers in Ethiopian shelter, survival is day to day

Image
MARTY NATHAN Meserat looks through her medicine supply in her streetside home. By MARTY NATHAN EDITOR'S NOTE: This is the second of a two-part series on street people in Hawassa, Ethiopia. The first article examined the plight of children. We learned of Qirchu, the Beggars' Village, from a woman I'll call Miriam, whom we met in front of St. Gabriel's Church on the square in downtown Hawassa, Ethiopia. My assistant Dagim and I had begun to interview children and women who begged on the streets of Hawassa, prompted by the stark image of homeless children sleeping in the gutters of the city's broad boulevards. Beggars have traditionally gathered on the premises of Ethiopia's Orthodox churches, where they are given food and clothes, particularly at holiday times, and are able to appeal to the parishioners on their way to services. The church reaches back to the fourth century and has a unique, Ethiopian-centered doctrine and ritual that sets it ap

Marty Nathan: Interviews reveal struggles of destitute in growing Ethiopian city

Image
A child in a beggars’ village area in Hawassa, Ethiopia. This is the first of a two-part series on street people in Hawassa, Ethiopia. The second article examines the plight of street women and explores local efforts to help the town confront the needs of beggars and homeless people. Early one morning I was riding my bike to work at the Referral Hospital in Hawassa, Ethiopia. My husband, Elliot Fratkin, and I had lived in the city for six months, sent on federal Fulbright grants to teach students at the University of Hawassa. He taught undergraduates at the main campus and I lectured and oversaw medical students and interns in the internal medicine department at the hospital. As I pedaled down a broad boulevard in this, the fastest-growing city in Ethiopia and a tourist center due to its location on a beautiful Rift Valley lake, I noticed two gaunt 6- or 7-year-old boys in tattered clothes and bare feet rising from under a gutter culvert. They stretched and climbed o

የኑሮ ውድነት ያሸበበው የበዓል ዋዜማ

Image
በታደሰ ገብረማርያም “የተለያዩ ዓይነት የምግብ ሸቀጦችና የእርድ እንስሳት ሥጋ ዋጋ ከአቅም በላይ ሆኗል፡፡ በአንፃሩ ደግሞ ገንዘብ የመግዛት አቅሙ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሽቆለቆለ ሲሔድ እንጂ ከወቅቱ የገበያ ሁኔታ ጋር ሲጣጣም አይታይም፡፡ በዚህም የተነሳ በክርስቲያንና በሙስሊሙ ኅብረተሰብ ዘንድ የሚከበረውን የዘመን መለወጫን የሚያክል ታላቅ በዓል በጥሩ ዝግጅት ለማሳለፍ ቀርቶ የዕለት ፍጆታን ለመሸፈን በማይቻልበት ደረጃ ላይ ተደርሷል፡፡ ይህ ዓይነቱ ሁኔታም በደሀና በሀብታም መካከል ያለው ክፍተት ከመጥበብ ይልቅ እየሰፋ መምጣቱን ለማወቅ የግዴታ የኢኮኖሚ ባለሙያ መሆን አይጠይቅም፡፡” ይህንን አስተያየት የሰነዘሩት በተለያዩ የገበያ ሥፍራዎች ለዘመን መለወጫ በዓል ቅቤና ዘይት፣ ዶሮ፣ በግ፣ እንቁላል፣ የጤፍና የስንዴ ዱቄት ሲሸምቱ ካገኘናቸው ወገኖች መካከል አንዳንዶቹ የበዓሉን ዝግጅትና የገበያውን ሁኔታ አስመልክተው በየተራ በሰጡት ማብራርያ ነው፡፡ እንደ አስተያየት ሰጪዎቹ አባባል ከሆነ በተለይ በምግብ ሸቀጦች ላይ የኢኮኖሚ አሻጥር የሚፈጽሙ ነጋዴዎች እየተበራከቱ መምጣታቸው መዘንጋት የለበትም፡፡ አሻጥር ከሚፈጽሙባቸውም የምግብ ሸቀጦች መካከል የምግብ ዘይትና ቅቤ፣ በአባይ ሚዛን የሚቸረችሩት ጥራጥሬዎችና የእህል ዱቄት፣ ሥጋ የመሳሰሉና ሌሎችም እንደሚገኙበት ጠቁመው ይህንን የሚከታተልና የሚቆጣጠር መንግሥታዊ አካል መኖሩን በመገናኛ ብዙኅን እንደሚሰሙ ይሁን እንጂ ይህ ዓይነቱ አካል በስም እንጂ በገቢር እንደማይታይና በአሻጥረኞችም ላይ ዕርምጃ ሲወስድ እንዳልተሰማ ወይም እንዳልታየ ነው ያስረዱት፡፡ ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ አምስት ነዋሪ የሆኑና መርካቶ ቅቤ ተራ ያገኘናቸው ወይዘሮ ሐረገወይን አበበ “ኑሮዬ መካከለኛ