የመላው ሲዳማ ሕዝብ ሕገ-መንግስታዊ ጥያቄ ምላሽ ሳያገኝ ትግሉ አይቆምም!!
ስማቸው እንዲገለጽ ካልፈለጉ የሲዳማ ታጋዮች የተላከ ጽሁፍ የመላው ሲዳማ ሕዝብ ሕገ - መንግስታዊ ጥያቄ ምላሽ ሳያገኝ ትግሉ አይቆምም !! ውድ የሲዳማ ሕዝብ ሆይ ! በቀደሙት ሳምንታት በሕዝባችን ላይ የተጫነውን የባርነት ቀንበር ለመታገል እንዲያስችሉ በማሰብ በርካታ መረጃ የሚያስጨብጡ ፅሑፎች ለንባብ መብቃታቸው ይታወሳል፡፡ ፅሑፎችም በይበልጥ ሕዝቡ ለነፃነቱ እንዴት መታገል እንዳለበት አቅጣጫ ከመጠቆም አልፎ የተለያዩ ወቅታዊ መረጃ የመስጠት ትልቅ ሚና ነበራቸው፡፡ የዚህ ፅሑፍ ዓላማም ከዚሁ የዘለለ አይሆንም፡፡ በዚህ መንግስት በሌለበት ሃገር ያለን ብቸኛ ሰላማዊ ትግል የማድረግ አማራጭ ስለሆነ !! የሐዋሳን ከተማ ከሲዳማ ሕዝብ እጅ ለመቀማት ( ወትሮስ የከተማዋን አብዛኛውን ክፍለ - ከተሞች ባለማወቅ ለአውሬዎች አሳልፈን ሰጥተን ነበር ) የተደረገው እኩይና አስነዋሪ የደኢህዴኖች ሴራ በሲዳማና በሲዳማ ሕዝብ ወዳጆች ልብ ውስጥ ከሃምሳ በላይ ወንድሞቻችንን፣ እህቶቻችንን፣ አባቶቻችንን በጠራራ ፀሐይ ካጣንበት የዛሬ 10 ዓመት ዘግናኝ ትዕይንት በላይ የጎዳንና ዛሬም የማይቀዘቅዝ ቁጣው ነግሶ ሰንብቷል፡፡ ለነሱ ሕዝቡ ውስጥ ለውስጥ ( ካድሬዎቻቸውም ጭምር ) እየሰራ ያለውን ስራ እንደቀድሞው የሲዳማ ሕዝብ አንዴ ሞቅ ብሎ ከ 3 ቀናት በኃላ ይቀዘቅዛል ከሚለው አዙሪታቸው ሳይወጡ አንድ ቀን በድንገት ፈንድቶ ታሪክ እንደሚለወጥና ውስጥ ለውስጥ እየሸረሸሩ የወሰዷቸውን በከተማም ሆነ ክልል ደረጃ የሚገኙ ቁልፍ ኃላፊነቶችን ተረክበንና ሕገ - መንግስታዊ መብታችንን አስከብረን በዓይናቸው የምናሳያቸው ቀን ቅርብ ነው፡፡ የጥፋት አጀንዳ አንግበው የመጡት ደኢህዴኖች ከጠበቁት በተቃራኒው የሲዳማ ሕዝብ ለነፃነቱ፣ ለአንድነቱና ለሕልውናው ታሪካዊ ትግል እንዲ