Posts

የመላው ሲዳማ ሕዝብ ሕገ-መንግስታዊ ጥያቄ ምላሽ ሳያገኝ ትግሉ አይቆምም!!

ስማቸው እንዲገለጽ ካልፈለጉ የሲዳማ ታጋዮች የተላከ ጽሁፍ የመላው ሲዳማ ሕዝብ ሕገ - መንግስታዊ ጥያቄ ምላሽ ሳያገኝ ትግሉ አይቆምም !! ውድ የሲዳማ ሕዝብ ሆይ ! በቀደሙት ሳምንታት በሕዝባችን ላይ የተጫነውን የባርነት ቀንበር ለመታገል እንዲያስችሉ በማሰብ በርካታ መረጃ የሚያስጨብጡ ፅሑፎች ለንባብ መብቃታቸው ይታወሳል፡፡ ፅሑፎችም በይበልጥ ሕዝቡ ለነፃነቱ እንዴት መታገል እንዳለበት አቅጣጫ ከመጠቆም አልፎ የተለያዩ ወቅታዊ መረጃ የመስጠት ትልቅ ሚና ነበራቸው፡፡ የዚህ ፅሑፍ ዓላማም ከዚሁ የዘለለ አይሆንም፡፡ በዚህ መንግስት በሌለበት ሃገር ያለን ብቸኛ ሰላማዊ ትግል የማድረግ አማራጭ ስለሆነ !! የሐዋሳን ከተማ ከሲዳማ ሕዝብ እጅ ለመቀማት ( ወትሮስ የከተማዋን አብዛኛውን ክፍለ - ከተሞች ባለማወቅ ለአውሬዎች አሳልፈን ሰጥተን ነበር ) የተደረገው እኩይና አስነዋሪ የደኢህዴኖች ሴራ በሲዳማና በሲዳማ ሕዝብ ወዳጆች ልብ ውስጥ ከሃምሳ በላይ ወንድሞቻችንን፣ እህቶቻችንን፣ አባቶቻችንን በጠራራ ፀሐይ ካጣንበት የዛሬ 10 ዓመት ዘግናኝ ትዕይንት በላይ የጎዳንና ዛሬም የማይቀዘቅዝ ቁጣው ነግሶ ሰንብቷል፡፡ ለነሱ ሕዝቡ ውስጥ ለውስጥ ( ካድሬዎቻቸውም ጭምር ) እየሰራ ያለውን ስራ እንደቀድሞው የሲዳማ ሕዝብ አንዴ ሞቅ ብሎ ከ 3 ቀናት በኃላ ይቀዘቅዛል ከሚለው አዙሪታቸው ሳይወጡ አንድ ቀን በድንገት ፈንድቶ ታሪክ እንደሚለወጥና ውስጥ ለውስጥ እየሸረሸሩ የወሰዷቸውን በከተማም ሆነ ክልል ደረጃ የሚገኙ ቁልፍ ኃላፊነቶችን ተረክበንና ሕገ - መንግስታዊ መብታችንን አስከብረን በዓይናቸው የምናሳያቸው ቀን ቅርብ ነው፡፡ የጥፋት አጀንዳ አንግበው የመጡት ደኢህዴኖች ከጠበቁት በተቃራኒው የሲዳማ ሕዝብ ለነፃነቱ፣ ለአንድነቱና ለሕልውናው ታሪካዊ ትግል እንዲ

Ethiopia’s Ruling Party to Meet Sept. 16 on Meles’s Successor

Image
By William Davison (Bloomberg) — Ethiopia’s ruling coalition will meet on Sept. 16 to select its chairman, who will replace the late Prime Minister, Meles Zenawi, as the party’s chief and probably succeed him as the Horn of Africa nation’s leader. Addisu Legesse, Hailemariam Desalegn, Bereket simon with their late chairman Meles Zenawi It’s “highly likely” the party chairman will become prime minister, State Minister for Communications Shimeles Kemal said by phone today from the capital, Addis Ababa. Meles, Ethiopia’s leader of 21 years who oversaw one of Africa’s fastest-growing economies, died on Aug. 20 from an infection contracted while recuperating from an undisclosed illness. Hailemariam Desalegn, Meles’s deputy, took over in an acting capacity the next day. “We are expecting the council meeting to be on the 16th,” Seikoture Getachew, the foreign relations head at the Ethiopian Peoples’ Revolutionary Democratic Front’s secretariat, said by telephone. “There will be

ለአህጉራዊ የየብስ ትራንስፖርት ትስስር ኢትዮጵያ የቤት ሥራዋን በማጠናቀቅ ዋዜማ ላይ ትገኛለች ፤ኢትዮጵያም የአፍሪካ አገራትን በየብስ ትራንስፖርት ለማገናኘት እየተገነቡ ካሉት ዘጠኝ ዋና መንገዶች የኬፕታውን-ካይሮ መንገድ ፕሮጀክት አካል የሆነውን የአዲስ አበባ-ናይሮቢ-ሞምባሳ አገናኝ መንገዶች ግንባታ ተያይዛዋለች። በዚህም መሰረት የዚህ ፕሮጀክት አገናኝ ለሆነው አዲስ አበባ-ሐዋሳ-ሀገረማርያም-ያቤሎ-ሜጋ-ሞያሌ መንገድ ግንባታ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶታል፡፡

የአፍሪካ አገራትን የንግድ ልውውጥ ለማፋጠን ፤ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ግንኙነትን የሚያጠናክሩና ድህነትን የሚቀንሱ በርካታ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛል፡፡ ይህን የአገራቱን ግንኙነት ለማጠናከርም ለመንገድ ልማት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት የ«ትራንስ አፍሪካን ሃይ ዌይስ»ፕሮጀክት ተቀርፆ ተግባራዊ እየሆነ ነው፡፡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፤ በ«ትራንስ አፍሪካን ሃይ ዌይስ" ፕሮጀክት የአህጉሪቱን ሀገሮች የሚያስተሳስሩ ዘጠኝ ዋና ዋና መንገዶች ይገነባሉ፡፡እነዚህም 56ሺ683ኪሎ ሜትር ይሸፍናሉ፡፡እነዚህ ዋና መንገዶች ከሰሃራ በታች በሚገኙ 41 ከተሞች የሚያልፉ ሲሆን፤ 500 ሚሊዮን ያህል ዜጎችንም ያገናኛሉ፡፡ የመንገዶቹ መገንባት የባህር በር ለሌላቸው አገራት የሚሰጠው ጠቀሜታም እጅግ የላቀ በመሆኑ መንገዱ በሚያልፍባቸው አካባቢዎች የሚገኙ አገራት የመንገዱ አካል የሆኑ መንገዶች በመገንባት ላይ ናቸው። ኢትዮጵያም የአፍሪካ አገራትን በየብስ ትራንስፖርት ለማገናኘት እየተገነቡ ካሉት ዘጠኝ ዋና መንገዶች የኬፕታውን-ካይሮ መንገድ ፕሮጀክት አካል የሆነውን የአዲስ አበባ-ናይሮቢ-ሞምባሳ አገናኝ መንገዶች ግንባታ ተያይዛዋለች። በዚህም መሰረት የዚህ ፕሮጀክት አገናኝ ለሆነው አዲስ አበባ-ሐዋሳ-ሀገረማርያም-ያቤሎ-ሜጋ-ሞያሌ መንገድ ግንባታ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶታል፡፡ የአዲስ አበባ-ናይሮቢ-ሞምባሳ መንገድ ፕሮጀክት አካል የሆነው የአዲስ አበባ-ሐዋሳ መንገድ በመጀመሪያው የመንገድ ልማት ዘርፍ መርሐ ግብር ከ10 ዓመት በፊት ተገንብቶ አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን፣94 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የሃገረማርያም-ያቤሎ መንገድም በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገነባ ይገኛል፡፡ ግንባታውም በግብፁ «ዓረብ ኮንትራክተርስ» እየተከናወነ ሲሆን፣ «ጓፍ ኢንጂነርስ አማካሪ መሐንዲሶች» ደ

የመለስ ኢትዮጵያና ወራሾቿ

Image
ፎቶ ኢንተርኔት በሰለሞን ጎሹ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ባረፉ በሁለት ሳምንታቸው ግብዓተ መሬታቸው ተፈጽሟል፡፡ ላለፉት ሁለት ሳምንታት በተለያዩ መንገዶች ሐዘን ከመግለጽ ጋር በተያያዙ እንቀስቃሴዎች ተወጣጥሮ የነበረው መንግሥት ወደ መደበኛው ሥራው እንደሚመለስ ይጠበቃል፡፡ የሥራዎቹ ሁሉ መጀመርያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀጣዩን ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲመርጥ ወይም የተመረጠውን ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲያፀድቅ ማድረግ ነው፡፡ በቀጣዩ ጠቅላይ ሚኒስትር ምርጫ ዙሪያ እየተደረጉ ያሉት የሐሳብ ልውውጦች ከጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የግል ሰብዕናና የፖለቲካ አመራር ብቃት፣ ከኢሕአዴግ የፖሊሲ ለውጥ የማምጣትና ያለማምጣት ጥያቄ፣ ከፓርቲ ፖለቲካውና ከዓለም አቀፍ ግንኙነት ጋር የተያያዙ ናቸው፡፡ ባለፉት 21 ዓመታት ኢትዮጵያን በፈለጉት መንገድ የቀረጿት ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ፣ የአገሪቱን ፖሊሲዎች በመንደፍ፣ አመራራቸውን ማዕከላዊ በማድረግ፣ በዓለም አቀፍ ግንኙነት ነጥረው በመውጣታቸው የተነሳ የተተኪውን ጠቅላይ ሚኒስትር ሥራ ከማክበዳቸውም በላይ፣ ኢትዮጵያውያን፣ የውጭ ዜጎችና መንግሥታት በቀጣይ ሥራዎች ላይ ጥያቄ እንዲያነሱ አድርጓል፡፡ የመለስ የአመራር ዘዬ መለስ ከልጅነታቸው ጀምሮ ብልህና ጎበዝ ተማሪ እንደነበሩ ስለእሳቸው የተጻፉ ሰነዶች ሁሉ ይመሰክራሉ፡፡ በአድዋም ሆነ በአዲስ አበባ ዊንጌት ትምህርት ቤት ያሉ መዛግብትም ይህን ያስተጋባሉ፡፡ ያቋረጡትን የሕክምና ትምህርትም በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ሲማሩም ጉብዝናቸው ተከትሏቸዋል፡፡ የ1960ዎቹ የተማሪዎች እንቅስቃሴ ከሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውና ከዩኒቨርሲቲ ተማሪነታቸው ጋር አብሮ በመሄዱ፣ የንባብ ፍላጎታቸው ከመደበኛው የትምህርት ጥናት ውጪ ወደ ፖለቲካው እንደተሸጋገረ ይ

ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመግቢያ ነጥብ ይፋ ሆነ መልካም እድል ለሲዳማ ተማሪዎች

Image
አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 2 (ኤፍ ቢ ሲ)አገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ በ2005 የትምህርት ዘመን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚገቡ ተማሪዎችን የመግቢያ ነጥብ ይፋ አደረገ፡፡ ሃገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ ለፋና ብሮድካስቲነግ ኮርፖሬት እንዳስታወቀው በ2005 የትምህርት ዘመንበከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን የሚከታተሉ ተማሪዎች 116, 651 ሲሆኑ ፥ ከእነዚህም መካከል 75 ሺህ 69 (64.35%) ወንዶች እና 41,582 (35.64%)  ያክሉ ደግሞ ሴቶች ናቸው። በተፈጥሮ ሳይንስ የትምህርት መስክ ለሁሉም መደበኛ ወንድ ተማሪዎች የመግቢያ ነጥብ 294 ሲሆን ፥ ለሴት ተማሪዎች ደግሞ 290 ሆኗል። ለታዳጊ ክልልና ለአርብቶ አደር ልጆች ወንድና ሴት ተማሪዎች 285 እና ከዚያ በላይ ሲሆን በተመሳሳይ ለግል ተፈታኞች ወንዶች 299 ለሴቶች 297 እና ከዚያ በላይ መሆኑን ገልጿል። በማኀበራዊ ሳይንስ የትምህርት መስክ ሁሉም ለመደበኛ ተማሪ ወንዶች 275 ፥ ለሴት ተማሪዎች ደግሞ 270 እና ከዚያ በላይ ሲሆን ፥ በዚሁ የትምህርት መስክ ለታዳጊ ክልልና ለአርብቶ አደር ልጆች ወንድ ተማሪዎች 270  ለሴት ተማሪዎች ደግሞ 268 እና ከዚያ በላይ ሆኗል።  መስማት ለተሳናቸው ተማሪዎች 270 እና ከዚያ በላይ እንዲሁም ለዓይነ ስውራን ተማሪዎች ደግሞ 230 እና ከዚያ በላይ እንደሆነም ኤጀንሲው አስታወቋል። እንዲሁም ለግል ተፈታኝ ወንድ ተማሪዎች 299 ለሴት ተማሪዎች ደግሞ 297 እና ከዚያ በላይ ውጤት ያስመዘገቡ ወደ ከፍተኛ ተቋማት እንዲገቡ መወሰኑን ገልጿል። በተመሳሳይም ወደ መሰናዶ የትምህርት መስክ የመግቢያ ነጥብ ለመደበኛና ለማታ ወንድ ተማሪዎች 2.57 ሲሆን ፥ ለሴት ተማሪዎች