ለአህጉራዊ የየብስ ትራንስፖርት ትስስር ኢትዮጵያ የቤት ሥራዋን በማጠናቀቅ ዋዜማ ላይ ትገኛለች ፤ኢትዮጵያም የአፍሪካ አገራትን በየብስ ትራንስፖርት ለማገናኘት እየተገነቡ ካሉት ዘጠኝ ዋና መንገዶች የኬፕታውን-ካይሮ መንገድ ፕሮጀክት አካል የሆነውን የአዲስ አበባ-ናይሮቢ-ሞምባሳ አገናኝ መንገዶች ግንባታ ተያይዛዋለች። በዚህም መሰረት የዚህ ፕሮጀክት አገናኝ ለሆነው አዲስ አበባ-ሐዋሳ-ሀገረማርያም-ያቤሎ-ሜጋ-ሞያሌ መንገድ ግንባታ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶታል፡፡
የአፍሪካ አገራትን የንግድ ልውውጥ ለማፋጠን ፤ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ግንኙነትን የሚያጠናክሩና ድህነትን የሚቀንሱ በርካታ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛል፡፡ ይህን የአገራቱን ግንኙነት ለማጠናከርም ለመንገድ ልማት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት የ«ትራንስ አፍሪካን ሃይ ዌይስ»ፕሮጀክት ተቀርፆ ተግባራዊ እየሆነ ነው፡፡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፤ በ«ትራንስ አፍሪካን ሃይ ዌይስ" ፕሮጀክት የአህጉሪቱን ሀገሮች የሚያስተሳስሩ ዘጠኝ ዋና ዋና መንገዶች ይገነባሉ፡፡እነዚህም 56ሺ683ኪሎ ሜትር ይሸፍናሉ፡፡እነዚህ ዋና መንገዶች ከሰሃራ በታች በሚገኙ 41 ከተሞች የሚያልፉ ሲሆን፤ 500 ሚሊዮን ያህል ዜጎችንም ያገናኛሉ፡፡ የመንገዶቹ መገንባት የባህር በር ለሌላቸው አገራት የሚሰጠው ጠቀሜታም እጅግ የላቀ በመሆኑ መንገዱ በሚያልፍባቸው አካባቢዎች የሚገኙ አገራት የመንገዱ አካል የሆኑ መንገዶች በመገንባት ላይ ናቸው። ኢትዮጵያም የአፍሪካ አገራትን በየብስ ትራንስፖርት ለማገናኘት እየተገነቡ ካሉት ዘጠኝ ዋና መንገዶች የኬፕታውን-ካይሮ መንገድ ፕሮጀክት አካል የሆነውን የአዲስ አበባ-ናይሮቢ-ሞምባሳ አገናኝ መንገዶች ግንባታ ተያይዛዋለች። በዚህም መሰረት የዚህ ፕሮጀክት አገናኝ ለሆነው አዲስ አበባ-ሐዋሳ-ሀገረማርያም-ያቤሎ-ሜጋ-ሞያሌ መንገድ ግንባታ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶታል፡፡ የአዲስ አበባ-ናይሮቢ-ሞምባሳ መንገድ ፕሮጀክት አካል የሆነው የአዲስ አበባ-ሐዋሳ መንገድ በመጀመሪያው የመንገድ ልማት ዘርፍ መርሐ ግብር ከ10 ዓመት በፊት ተገንብቶ አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን፣94 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የሃገረማርያም-ያቤሎ መንገድም በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገነባ ይገኛል፡፡ ግንባታውም በግብፁ «ዓረብ ኮንትራክተርስ» እየተከናወነ ሲሆን፣ «ጓፍ ኢንጂነርስ አማካሪ መሐንዲሶች» ደ