Posts

የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር /ኢሕአዴግ/ ሥራ አሥፈፃሚ ኮሚቴ ነገ ይሰበሰባል

Image
አዲስ አበባ ነሐሴ 28/2004 የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር /ኢሕአዴግ/ ሥራ አሥፈፃሚ ኮሚቴ ነገ ማክሰኞ መደበኛ ስብሰባውን ያካሂዳል፡፡ በነገው ዕለት በሚከፈተው የግንባሩ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ አፈፃጸምን ይዳስሳል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ኮሚቴው የ2004 በጀት ዓመት አፈፃጸሞችን በጥልቀት በመፈተሽ የግንባሩ ሊቀመንበር የነበሩትና የባለ ራዕዩና ታላቁ መሪ የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ህልፈት ተከትሎ በሰፊው የኢትዮጵያ ሕዝብ የተስተጋባውን ቁጭትና እልህ በልማት ላይ በሚቻልበት ሁኔታ እንደሚነጋገር ለማወቅ ተችሏል፡፡ የታላቁን መሪውና በእሳቸው የተገነባውን የግንባሩና የአገሪቱ ልማታዊ መንግሥት ራዕይ ሁሉም በየተሰማራበት የስራ መስክ በመረባረብ ለማስቀጠል የገባውን ቃልና መነሳሳት የሚመጥን ዝግጅት ማድረግ በሚቻልባቸው ዙሪያም ኮሚቴው ይመክራል፡፡ በተጨማሪም ከኮሚቴው አባላት በሚነሱ አጀንዳዎች ዙሪያ በመምከር ውሳኔዎችን እንደሚያሳልፍ ይጠበቃል ሲል ኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል፡፡ http://www.ena.gov.et/story.aspx?ID=2329

Desecuritising quest for regional self-administration in Sidama-land

BY  Mulugeta Daye 8 hours ago  · (ከማህበራዊ መረብ ላይ የተገኘ ጽሁፍ) I am learning form the reports from the Sidama-land the reason Iyasu Ragaasa, Dukk’ale Lamiso, Boshla Gabiso, Abate Kimmo, et al jailed, they are alleged to mobilise people against government. If the allegations are correct, and even if those jailed people involved in mobilization of the Sidama-for regional self- administration. The commitment of late Prime-Minster Meles Zenawi to give constitutional guarantee to the Nations, Nationalities, and Peoples, to opt out from the Union which they are uncomfortable with as it is enshrined in article 39 of Ethiopian constitution, has become invalid while this visionary is in hospital bed. In the movement of 2005-2006 he legitimised the Sidama’s quest for regional autonomy. However he come down to the Sidama-land, capital and politely advised the nation to choose regional autonomy or development. For the Sidama both Regional autonomy and Development are the same thing. Because withou

ወ/ሮ አዜብ አቶ መለስን ለመተካት እየታገሉ ነው

Image
ነሀሴ ፳፰ (ሀያ ስምንት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ወ/ሮ አዜብ መስፍን ባለቤታቸውን በሞት ካጡ በኃላ በእሳቸው እግር ተተክተው የህወሃትን የሊቀመንበርነት ቦታ ተቆናጥጦ ወደ ኢህአዴግ ምክትል ሊቀመንበርነት ለመሳብ ድጋፍ የማሰባሰብ ዘመቻ ላይ መክረማቸውን ምንጮቻችን ጠቆሙ፡፡ በኢህአዴግ 36 የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ውስጥ ብቸኛ ሴት ሆነው በመስከረም ወር 2003 ዓ.ም ከፍተኛውን የፓርቲ ሥልጣን በባለቤታቸው በአቶ መለስ ዜናዊ ልዩ ድጋፍ ማግኘት የቻሉት ወ/ሮ አዜብ የሰሞኑን ሐዘናቸውን ለድጋፍ ማሰባሰቢያ እንደተጠቀሙበት ምንጮቻችን ተናግረዋል፡፡ ወ/ሮ አዜብ ለድጋፍ ማሰባሰቢያ ይጠቅሙኛል የሚሉዋቸው የህወሃት ሰዎች ለቅሶ ለመድረስ ቤተመንግስት በሚመጡበት ወቅት አንገታቸውን እያነቁ በማልቀስና በማስለቀስ፣የማይፈልጉዋቸውን ደግሞ ፊት ሲነሱ መቆየታቸው በተለይ በአመራር ላይ ባሉት የብአዴን ሰዎች ዘንድ አልተወደደላቸውም፡፡ ወ/ሮ አዜብ ባለቤታቸው አቶ መለስ በ8ኛ ድርጅታዊ ጉባኤ በጡረታ ያሰናበታቸው አቶ ሥዩም መስፍን፣አቶ አባይ ጸሐዬ፣አቶ አርከበ ዕቁባይ፣አቶ ተፈራ ዋልዋ፣አቶ አዲሱ ለገሰን “የመለስን ራዕይ ለማሳካት” በሚል ስትራቴጂ ከጎንዋ ለማሰለፍ ከፍተኛ ጥረት ሲያደርጉ መሰንበታቸውን ምንጮቹ ገልጸዋል፡፡ ወ/ሮዋ በአቶ መለስ ቀብር ፕሮግራም ላይ በወ/ሮ ነጻነት አስፋው የተዘጋጀላቸውን ኦፊሻል ንግግር በመተው የራሳቸውን ኃሳብ ያንጸባረቁበት ንግግራቸው “መለስ የጀመራቸው ፖሊሲና ስትራቴጂዎች እስካልተበከሉና እስካልተበረዙ ድረስ …” የሚለው ንግግራቸው በመለስ ስም ለጀመሩት የድጋፍ ማሰባሰብ ጥረታቸው ይረዳቸው ዘንድ ሆን ብለው ያደረጉት መሆኑን ምንጫችን  አስቀምጦአል፡፡ የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች ከዚህ ሳምንት ጀምሮ ጉባኤያቸ

የሲዳማን የክልል ጥያቄ በማቀጣጠል ይሰሩ ከነበሩት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መካከል ኣንዳንዶቹ ጸረ የሲዳማ ክልል ኣቋም ካላቸው ግለሰቦች ጎራ እየተቀላቀሉ መሆኑ ተሰማ

Image
የሲዳማ የክልል ጥያቄን በተደራጀ መልኩ ለማቅረብ የብሄሩን ሽማግሌዎች በመደራጀት እና የክልል ኣስፈላጊነትን በተመለከተ ለህዝቡ በማስረዳት ከፍተኛ የሆነ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ በዩኒቨርስቲ ተመሪዎች ስሰራ መቆየቱ የሚታወስ ሲሆን፤ ግንዛቤ የመፍጠር ኃላፊነት ወስደው በመስራት ላይ ከነበሩት ወጣቶች መካከል ኣንዳንዶቹ በግልጽ ባልታወቀ ምክንያት ቡድኑን በመልቀቅ ላይ ናቸው። ስማቸው እንድገለጽ ያልፈለጉ የሲዳማ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ለወራንቻ ኢንፎርሜሽን ኔትዎርክ እንደተናገሩት፤ ጸረ የሲዳማ ክልል ኣቋም ያላቸው ግለሰቦች ኣንዳንድ ተማሪዎችን በገንዘብ በመደለል እና በማስፈራራት በሲዳማ የክልል ጥያቄ ላይ ያላቸውን ኣቋም እንዲቀይሩ በማድረግ ላይ ናቸው። እነዚሁ በገንዘብ ተደልለው ጸረ የሲዳማ ክልል ኣቋም ካላቸው ቡድኖች ጎን የተቀላቀሉት የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ሌሎች ከዚህ ቀደም ኣብሯቸው ሲታገሉ የነበሩት በማጋለጥ እና በማሳሰር ላይ ናቸው ብለዋል። ለኣብነትም የሲዳማን ሽማግሌዎች በማደረጀት ከፍተኝ ሚና ከተጫዎቱች ተማሪዎች መካከል ሁለቱ በቅርቡ መታሰራቸውን ኣመልከተው፤ የተቀሩትም በመፈለግ ላይ መሆናቸው ተናግረዋል።

በፊቼ ማግስት በወንዶ ገነት ወረዳ ከታሰሩት ወጣቶች መካከል 12ቱ እንደታሰሩ መሆናቸው ተገለጸ

በወንዶ ገነት ወረዳ በፊቼ ማግስት የሲዳማን የክልል ጥያቄ የሚያወድሱ ግጥሞችን እየገጠሙ ቄጣላ የወጡ ወጣቶች በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ታፍሰው መታሰራቸው የሚታወስ ሲሆን፤ ከታሰሩት ወጣቶች መካከል 12 ቱ እስከ ኣሁን ኣልተፈቱም። ወጣቶቹ እስከ ኣሁን ድረስ ለምን እንደታሰሩ የሚገልጽ ምንም መረጃ የሌላቸው ሲሆን፤ የታሰሩበትን ምክንያት በይፋ እንደማያቁ እና ዛሬ ነገ ትፈታላችሁ እየተባሉ በእስር ላይ እንደምገኑ ገልጸዋል።