Posts

የጠቅላይ ሚኒስትሩን የዕድገትና የልማት ጅማሮዎች ኢሕአዴግ ለሕዝብ ግንኙነት ሥራ አልተጠቀመበትም ተባለ

Image
በታምሩ ጽጌ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ከትግል አጋሮቻቸው ጋር በመሆን ደርግን ከጣሉ ማግስት ጀምሮ፣ በአገር ዕድገትና ልማት ሥራ ላይ የተሰማሩ ቢሆንም፣ ኢሕአዴግ ለሕዝብ ግንኙነት ሥራ እንዳልተጠቀመበት አስተያየት ሰጪዎች እየገለጹ ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በ1986 ዓ.ም. በአማራና በኦሮሚያ የተለያዩ የገጠር ቀበሌዎች በመዘዋወር ያደርጉዋቸውን ጉብኝቶች የሚያስቃኝ ዘጋቢ ፊልም ሰሞኑን በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የተመለከቱት አስተያየት ሰጪዎች፣ ኢሕአዴግ በሕዝቡም ሆነ በተቀናቃኝ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚደርስበትን ትችት የሚያስተባብል ሆኖ እንዳገኙት ተናግረዋል፡፡ ኢሕአዴግ በምርጫ ሰሞን “ልማት፣ ልማት የሚለው ሕዝቡን ለማታለልና ያልሠራውን ሥራ በመደርደር ነው፤” በማለትና በመግለጽ ሲቃወሙት የነበሩትን የውጭና የአገር ውስጥ ድርጅቶች ያስታወሱት አስተያየት ሰጭዎቹ፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እላይ ካለው የመንግሥት ባለሥልጣን እስከታችኛው አርሶ አደር ድረስ ለልማት ሲያደርጉት የነበረውን ጥረት ለሕዝብ ይፋ አለመደረጉ ለትችት እንዳጋለጠው ገልጸዋል፡፡ ሰሞኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሥልጣን ዘመናቸው የሠሩዋቸውን የቅርብ ጊዜና ከድል ማግስት ያደርጓቸው የነበሩትን የዕድገትና የልማት እንቅስቃሴዎች የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ሲያስተላልፍ የተመለከቱት አስተያየት ሰጭዎቹ፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሠርተዋቸው ያለፉት ሥራዎች የበለጠ የሚያስወድዳቸውና ይቃወማቸው የነበረውን ሁሉ ተቃውሞውን እንዲያነሳ የሚያደርጉ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ኢሕአዴግ በተለይ በምርጫ ሰሞን እታች ወርዶ ቢሠራ ከዓለም አቀፎቹ ሂዩማን ራይትስ ዎች፣ አምነስቲ ኢንተርናሽናልና ከሌሎች አገር አቀፍ ድርጅቶች ትችት ከመዳኑም በተጨማሪ፣ አብዛኛዎቹን የአገሪቱን ዜጐች የኢሕአዴግ ደጋፊ ሊያደርግ የሚያስችለው እንደነበር አውስተዋል፡

የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሥርዓተ ቀብር ተፈጸመ

Image
አዲስ አበባ ነሐሴ 27/04-የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሥርዓተ ቀብር ዛሬ ከቀኑ 9ሰዓት ከ15 ላይ ተፈጸመ። የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ አስከሬን ከመስቀል አደባባይ በአገር መከላከያ ሠራዊት በክብር ታጅቦ ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ከደረሰ በኋላ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የጸሎት ሥነ-ሥርዓት ተደርጎለታል። የጸሎት ሥነ-ሥርዓቱ እንደተጠናቀቀ የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ አስከሬን ግብዓተ መሬት ሲፈጸም 21 ጊዜ መድፍ ተተኩሷል። ሥርዓተ ቀብሩ ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ፣ሚኒስትሮች፣የሕዝብ ተወካዮችና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች አፌ ጉባዔዎች፣ የክልል ርዕሳነ መስተዳድርና የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ተወካዮች፣በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ተገኝተዋል። ቀደም ሲል በመስቀል አደባባይ ከ700 በላይ ልዑካንን ያካተተ ከ25 በላይ አገሮች መሪዎች፣ ርዕሳነ ብሔራትና የበርካታ አገሮች ባለሥልጣናት፣የአገሪቱ ከፍተኛ ባለሥልጣናትና ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሕዝብ ተገኝቶ የጠቅላይ ሚኒስትር መለስን አስከሬን ተሰናብቷል። በሥነ-ሥርዓቱ ላይ በማደግ ላይ የሚገኙ ክልሎችና የሲቪክ ማህበራት ተወካዮች፣ በተባበሩት መንግስታት የአሜሪካ መንግሥት ቋሚ ተወካይ አምባሳደር ሱዛን ራይስ፣ የቤኒን ፕሬዚዳንትና የወቅቱ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር ዶክተር ቦኒ ያዬ ንግግር አድርገዋል። እንዲሁም የዑጋንዳው ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ፣ የሩዋንዳው ፕሬዚዳንት ፖል ካጋሚ፣ የደቡብ አፍሪካው ፕሬዚዳንት ጃኮቭ ዙማና የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ሚያርዴት በተመሳሳይ ንግግር ማድረጋቸውን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል። ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት በ57

በሐዋሳ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲታከሙ አስመስለው የተነሱ ፎቶዎችን ሲሸጡ የተገኙ በፖሊስ ተያዙ፤በሐዋሳ ከተማ ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ ነዋሪዎች እንዲሁም እሑድ የሲዳማ ብሔረሰብ አባላት በባህላዊ ሥርዓት ሐዘናቸውን በገለጹባቸው ቀናት በርካታ ፎቶ ግራፎችና ፖስተሮች የተሸጡ ሲሆን፣ ሁለቱ ግለሰቦች የጠቅላይ ሚኒስትሩን የተሳሳቱ ፎቶ ሲሸጡ መያዛቸውን የፖሊስ ኃላፊው አስረድተዋል፡፡

Image
በሐዋሳ ከተማ የጠቅላይ ሚኒስትር  መለስ ዜናዊ ሕልፈተ ሕይወት ከተነገረበት ቀን ጀምሮ በርካታ ፎቶግራፎች ሲሸጡ የሰነበቱ ሲሆን፣ በሕክምና ላይ እያሉ አስመስለው የተነሱ ፎቶግራፎችን ሲሸጡ የተገኙ ግለሰቦች ደግሞ በፖሊስ ተይዘዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሆስፒታል ውስጥ ጉሉኮስ ተደርጎላቸው የተነሱ አስመስለው በማሳተም በተለይ መስቀል አደባባይ በሚባለው አካባቢ ፎቶግራፉን በአምስት ብር ሲሸጡ፣ ትክክለኛ መስሎአቸው ነዋሪዎች እየተሻሙ ሲገዙ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል፡፡  ይሁንና ፖሊስ በደረሰው ጥቆማ መሠረት ሁለት ሰዎች በዚህ ድርጊት  ምክንያት ከቁጥጥር ሥር ሲውሉ፣ ሕገወጥ ፎቶዎችን በማሰራጨት ድርጊት ተጠያቂ ተደርገው በፖሊስ ጣቢያ መታሰራቸውን የሐዋሳ ከተማ ፖሊስ መምርያ አስታውቋል፡፡  ስሙን መጥቀስ ያልፈለገ አንድ ፎቶግራፍ ሲሸጥ የነበረ ወጣት ጠቅላይ ሚኒስተሩ በሕክምና ላይ እያሉ የሚያሳየውን ፎቶግራፍ ከየት እንዳገኙት ተጠይቆ፣ ‹‹እኔ ያንን ፎቶ አላገኘሁትም፣ ነገር ግን ሲሸጡ የነበሩት ሰዎች ከኢንተርኔት እንዳገኙት ሰምቻለሁ፤›› በማለት ለሪፖርተር ተናግሯል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉሉኮስ ተሰጥቶአቸው ተኝተው ሲታከሙ የሚያሳየውን ፎቶግራፍ ትክክለኛ መስሎዋቸው እንደገዙ የገለጹት የሐዋሳ ነዋሪ የሆኑት አቶ ዳንጊሶ ተሰማ፣ ‹‹ሐሰተኛ መሆኑን  ባውቅ አልገዛውም ነበር፤›› ብለዋል፡፡ ስለጉዳዩ የሐዋሳ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ወንጀል መከላከል የሥራ ሒደት ኃላፊ ኢንስፔክተር ታደሰ በንቲ ተጠይቀው፣ ጠቅላይ ሚኒስተሩ በሕክምና ላይ እያሉ አስመስለው  የተነሱትን ፎቶግራፎች በማተም ሲሸጡ የነበሩ  ሁለት ሰዎች በመናኸሪያ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ መታሰራቸውን ጠቁመው፣ ሌሎች ፎቶግራፎችና ፖስተሮችን እየሸጡ በሚገኙት ላይም ክትትል እየተደረገ መሆኑን ለሪፖርተር አስ

Human Rights Violations in Sidama Escalating

Image
New August 31 2012-Arrest and abduction have been commonplace occurrences in Sidamaland and it has been worsened since last June when Sidama public pressed the demand of regional Self adminstration right. Since then, many innocent Sidamas are languishing in jails illegally and whereabouts of many are unknown. Fabricated charges are used against those who are imprisoned as means to lock them up indefinitely. For instance, Ougamo Hanaga, who is an employee of Save the Children Awassa branch, made the following comment on facebook about the ordeal of innocent Sidamas and he was arrested few days later. He then charged with terrorism under the country's antiterrorism law without hard evidence that links him to terrorism. http://sidamaliberation-front.org/

A Shadow Government set to rule Post-Meles Ethiopia

Image
As expected, although they have no choice but to elevate Hailemariam Desalegn formally to replace Meles’ position, the ruling elites have formed a shadow government that will make all the real decisions  behind the scenes. This shadow government – a “transition time caretaker” – is made up of seven members. According to individuals privy to the process of selection, the justification given for the appointment is that the shadow government should be made up of one person from each of EPRDF’s member parties, and one each from key government agencies – intelligence, foreign affairs, and the military. Below is the list. Name Representing Parent Party Ethnicity General Se'are Mekonnen Military TPLF Tigrean Getachew Assefa Intelligence TPLF Tigrean Berhane Gebrekiristos Foreign Affairs TPLF Tigrean Seyum Mesfin TPLF TPLF Tigrean Bereket Simon ANDM ANDM Tigrean (Eritrean) Kuma Demeksa OPDO OPDO Unknown (Tigrean/Amhara) Hailemarim Desalegn SEPDM SEPDM Walayta It is asto