Posts

የኢትዮጵያን የውክልና ሕግ ቢያውቁ ይጠቀማሉ

በኤልያስ ዶጊሶ  ከደቡብ ክልል ፍትህ ቢሮ  እጅግ እየዘመነ በመጣው የዓለማችን የኑሮ ሁኔታ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የሕልውና ጥያቄ ሆኗል። በተለይ ሕዝቦች ከከፋ ድህነት ተላቅቀው የተሻለ ሕይወት መምራት እንዲችሉ በኢኮኖሚው መስክ ንቁ እንቅስቃሴ እንዲያደርጉ ይጠበቃል፡፡ እንደ ንግድ ያሉ የኢኮኖሚ ዘርፎች ደግሞ አንዳንዴ በተመሳሳይ ቀንና ሰዓት የተለያየ ስፍራ መገኘትን ይጠይቃል። የሰው ልጅ ደግሞ በተፈጥሮው በጊዜና በቦታ ውሱን ከመሆኑ አንፃር በተመሳሳይ ቀንና ሰዓት ጥቅሙን በሚመለከቱ ስፍራዎች ሁሉ ተገኝቶ ተግባሩን መከወን አይችልም፡፡ እነዚህ መሰል ጉዳዮችን አስመልክቶ የሰው ልጅ የሚኖረው ብቸኛ አማራጭ እንደራሱ ሆኖ በእርሱ እግር ተተክቶ ጉዳዮቹን ወይም ሥራዎቹን የሚከውንለትን ሰው መወከል ግድ ይሆንበታል፡፡ ሥራዎችን በውክልና ማሰራት አስፈላጊ የሆነው በኢኮኖሚው ዘርፍ ብቻ ሳይሆን በማህበራዊ የሕይወት መስክም ካለው ጠቀሜታ አኳያ ነው፡፡ በየትኛውም ዘርፍ የሚደረጉ የውክልና ውሎች ማዕቀፋቸው በፍትሐብሔር ሕግ ከአንቀጽ 2179 እስከ 2285 ባሉ ድንጋጌዎች ነው፡፡ በዚሁ ሕግ መሠረት የውክልና ሕግ የእንደራሴነት ሕግ ተብሎ የሚጠራ ሲሆን ሁለቱንም ቃላት መጠቀም በፍቺ ረገድ ልዩነት የላቸውም፡፡ በአማርኛ መዝገበ ቃላት «ወኪል» የሚለውን ቃል እንደዋና ሆኖ የሚሰራ፣ ተጠሪ፣ ኃላፊ፣ ዋናውን ተክቶ እንዲሰራ የተመረጠው ሰው፣ አካል የሚል ሲሆን «ውክልና» ማለትን ደግሞ ለአንድ ሰው ወይም ድርጅት ወኪል፣ ተጠሪ መሆን የሚል ፍቺ ተሰጥቶታል፡፡ በፍ/ሕ/ቁ 2199 መሠረት ደግሞ «ውክልና» ማለትን በሚከተለው መልኩ ይተረጉመዋል፡፡ «ተወካይ የተባለ አንድ ሰው ወካይ ለተባለው ሰው እንደራሴ ሆኖ አንድ ወይም ብዙ ሕጋዊ ሰራዎችን በወካዩ ስም ለማከናወን ግዴታ የሚገባበት ውል ነው።

ኣስቂኝ ዜና ስለ ኣቶ መለስ እና የፕሬስ ነጻነት

Image
በተለይ በላፉት ኣምስት ኣመታት የሚዲያ ነጻነት ኣፊነው ጋዜጤኞችን በየጊዜው በሰበብ ኣስባቡ ከከርቼሌ ዘብጥያ ስወረውሩ የቆዩትን መሪ ለሚዲያ ነጻነት ታግለዋል ብሎ የሚያወድስ ዜና መስማት ኣያስቂም? ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የፕሬስ ነፃነት እንዲከበር ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክተዋል  -የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለሥልጣን አዲስ አበባ፡- የኢትዮጵያ ብሮድ ካስት ባለስልጣን ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በኢትዮጵያ የፕሬስ ነፃነት እንዲከበር ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱ መሪ እንደነበሩ ገለጸ። ባለሥልጣኑ ለዝግጅት ክፍላችን በላከው መግለጫ የባለስልጣኑ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሞት ጥልቅ ኀዘን እንደተሰማቸው ገልጿል።  ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ቤተሰቦችና ለኢትዮጵያ ህዝብም መጽናናትን ተመኝቷል።  ጠቅላይ ሚኒስትሩ የዜጎች ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ህገ መንግሥታዊ ዋስትና አግኝተው ተግባራዊ እንዲሆኑ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን ባለሥልጣኑ ገልጿል። በኢትዮጵያ የፕሬስ ነፃነት እንዲከበር ማድረግ የአመለካከት እና ሀሳብን በነፃ የመያዝና የመግለጽ መብት እውን እንዲሆን ሰርተዋል ብሏል። አገሪቱ ከኋላ ቀርነት እና ከድህነት ተላቅቃ በአፍሪካም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ስሟ በመልካም እንዲጠራ የሰሩ እሩቅ አሳቢና ባለዕራይ ነበሩ። ያለው የባለሥልጣኑ መግለጫ፣ እሳቸው የጀመሩትን የሰላም የልማትና የዴሞክራሲ መስመር በመከተል ለማሳካት ጠንክሮ እንደሚሰራ አረጋግጧል። http://www.ethpress.gov.et/ethpress/main/news.php?newsLocation=home&newsInstruction=headline&newsId=9252

Food Production and Food Losses

People in all over the world produce their foods in their own peculiar way and system of production. The way an American farmer grows food compared with their Ethiopian counterparts are beyond comparison. The number of people who are engaged in agriculture in America is said to be only three percent of the total population while 87pct of the Ethiopian population are agriculturalists. However, the American farmers are net food exporters contrary to the large majority Ethiopians who are subsistence farmers and food insecure. This is not God’s curse against the Ethiopians; rather it is the huge difference in their level of development and production systems.  As in their food production, there is also marked difference between America and Ethiopia in the amount of their food losses. The amount of food losses in America is so large that it is incomparable with the food Ethiopia loses which is very minimal. The same is true with America and other developing countries. The same reality is a

Hawassa University Expresses its grief on the death of our late Prime Minister His Excellency Mr. Meles Zenawi. The University wishes strength for his family and the Ethiopian People.

Image
продвижение сайтов Hawassa University Expresses its grief on the death of our late Prime Minister His Excellency Mr. Meles Zenawi. The University wishes strength for his family and the Ethiopian People.

በኢትዮጵያ ህይወት ብርሃን ቤተክርስቲያን የደቡብ ኢትዮጵያ ህብረት ጽህፈት ቤት ፣ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የሀዋሪያት ቤተክርስቲያን ተማሪዎች ህብረት፣ የሀዋሣ ጐተራ ቃለ ህይወት ቤተክርስቲያን ጽህፈት ቤት በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሞት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገለፁ፡፡

  በኢትዮጵያ ህይወት ብርሃን ቤተክርስቲያን የደቡብ ኢትዮጵያ ህብረት ጽህፈት ቤት ፣ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የሀዋሪያት ቤተክርስቲያን ተማሪዎች ህብረት፣ የሀዋሣ ጐተራ ቃለ ህይወት ቤተክርስቲያን ጽህፈት ቤት በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሞት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገለፁ፡፡ ክቡር ጠቅላይ ሚኒሰትሩ የሀገራችን የልማት ሀዋሪያ፣ የምን ጊዜም ጀግና ፣ የፍሪካ ኩራት ናቸው፡፡ በሞት ቢለዩንም ህያው ሥራዎቻቸው በኢትዮጵያውያን ልብ ሲታወሱ ይኖራሉ ብለዋል፡፡   ለሀይማኖት መስፋፋት፣ ነፃነትና እኩልነት የተጉ መሪ እንደነበሩ ያመለከቱት መግለጫ ሰጪዎች በክልሉ የሚገኙ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች እጅ ለእጅ ተያይዘን የተጀመሩ የልማት ተግባራትን ከዳር ለማድረስ ቆርጠን እንሠራለን ብለዋል፡፡ http://www.smm.gov.et/_Text/21NehTextN604.html  

የሲዳማ ዞን ሴቶች ህፃናትና ወጣቶች መመሪያ፣ የእዥ ወረደ አስተዳደር በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሞት የተሰማቸውን ሐዘን ገልፀዋል፡፡

ክቡር ጠቀላይ ሚኒስትር የሴቶችንና የወጣቶችን ተሳታፊነትና ተጠቃሚነትን እንዲሁም የህፃናትን መብትና ደህንነት ለማስጠበቅ ምቹ የሆኑ ፖሊሲዎችንና ስትራቴጂዎችን በመንደፍና ተግባራዊ በማድረግ ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ ችለዋል፡፡ በርሳቸው አመራር ኃላ ቀርነትን ታሪክ ለማድረግና የበለፀገች ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚያስችል መሠረት ተጥሏል፡፡ ይሁን እንጂ ባጋጠማቸው ድንገተኛ ሞት የከፋ ሀዘን ተሰምቶናል ብለዋል፡፡   በተመሳሳይ የሀዋሳ እርሻ ልማት ድርጅትና የኢትዮጵያ መፅሐፍ ቅዱስ ማህበር ሀዋሣ ቅርንጫፍ ሀገራችንን በበሳል አመራር ላለፉት 21 አመታት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ በመምራትና ትክክለኛ የእድገት መንገድ በመቀየስ መሪ ሚና የተጫወቱት ክቡር ጠቅላይ ሚኒሰትር በመለየታቸው ጥልቅ ሀዘን እንደተሰማቸው አመልክተዋል፡፡ http://www.smm.gov.et/_Text/21NehTextN204.html

የሲዳማ ሕዝብ የሀገር ኩራት በሆነው በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሞት የተሰማውን መሪር ሀዘን ሲገልጽ ለመላዉ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲሁም ለቤተዘመዶቹ መጽናናትን በመመኘት ነዉ !! ይሁንና በርካታ የሲዳማ ብሔር ተወላጆች በማይታወቅ ምክንያት ታስረዉ ይሄን ብሔራዊ ሀዘን ለመካፈል ባለመቻላቸዉና የዋስ መብት እንኳን በመነፈጋቸዉ እሮሮአቸዉን በማሰማት ላይ ይገኛሉ፡፡ (ከማህበራዊ መረብ ላይ የተገኘ ጽሁፍ)

Image
የሲዳማ ሕዝብ የሀገር ኩራት በሆነው በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሞት የተሰማውን መሪር ሀዘን ሲገልጽ ለመላዉ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲሁም ለቤተዘመዶቹ መጽናናትን በመመኘት ነዉ !! ይሁንና በርካታ የሲዳማ ብሔር ተወላጆች በማይታወቅ ምክንያት ታስረዉ ይሄን ብሔራዊ ሀዘን ለመካፈል ባለመቻላቸዉና የዋስ መብት እንኳ በመነፈጋቸዉ እሮሮአቸዉን በማሰማት ላይ ይገኛሉ፡፡  በሕገ-መንግስቱ በአንቀጸ 39 ላይ የተደነገገውን መብት እስክንጎናጸፍ ድረስ የማንነት ጥያቄአችን ከምንም ጊዜ በላይ ተጠናክሮ ይቀጥላል፤ በምንም ዓይነት ሁኔታ አይቆምም!!! ውድ የሲዳማ ብሄር ተወላጆች በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ የምትገኙ በሙሉ እንኳን በዓይነቱ ልዩ ለሆነውና በሲዳማ ታሪክ የመጀመሪያ ሊባል ለሚገባው ለ2005 ዓ.ም ሲዳማ የዘመን መለወጫ fichee cambalaalla በዓል ለማየት፣ለመስማት አበቃችሁ/ በሰላም አደረሳችሁ/ን/!!  የሲዳማ ዘመን መለወጫ የfichee cambalaalla በዓል ነሐሴ 9/2004/ በሲዳማ ቀን አቆጣጠር መስከረም 1/ 2005 ዓ.ም በአስገራሚ ሁኔታ ከዚህ ቀደም በታሪክ ታይቶና ተሰምቶ በማይታወቅ መልኩ በዓሉን ለማክበር ከየአቅጣጫዉ ወደ ሀዋሳ የመጡት የብሔሩ ተወላጆች ብቻ ሌሎች ታዳሚዎችን ሳይጨምር በጥቂቱ ቁጥራቸው ወደ 2.5ሚሊየን የሚጠጉ በባህላዊ አጋጌጥ ተውበው ጦርና ጋሻቸውን አንግበው በዋና ከተማቸው በድምቀት ለማክበር በቄጣላ በመግባታቸው የከተማውን ሕዝብ ጉድ ያስባለና ያስደነቀ ታሪካዊ በዓል መሆኑ ይታወሳል፡፡  በዕለቱም ሰፊው የሲዳማ ሕዝብና የበዓሉ ታዳሚዎች/ተጋባዥ እንግዶች በዓሉን እንደጓጉለት ለማክበር አልታደሉም፡፡ በዓሉን ለማክበር የወጣውን የሕዝብ ብዛት ከሩቁ የተመለከቱና ከየአቅጣጫው በቄጣላ የዘመኑ የሙዚቃ ቅንብር በማይተካ መ