Posts

SLF Statement on the Death of Meles Zenawi

August 22 2012-The 21 years of Meles Zenawi’s rule were continuation of brutalization and suffering of Sidamas people that have even worsened during his iron-fisted rule.  Now, Meles is gone, but the system he championed has continued preying on Sidama innocents. Even, as he was fighting for his life at undisclosed location, hundreds of Sidamas were unlawfully arrested and thrown into jails. The army that was deployed throughout the Sidama has continued intimidation and terrorizing Sidama people. The former president of South Nation Nationalities and People Regional Government and possible successor of Meles Zenawi, Hailemariam Desalegn, is the main architect of Loqqe massacre, one of worst atrocities ever committed on sidama soil. He is also behind ill-devised policies that targeted Sidama for past 10 years.  The demise of Meles Zenawi may open window of opportunity to end the suffering of people in Ethiopia if the ruling party were to stop pursuing the same failed policy of past tha

የኣቶ መለስ ዜናዊን ሞት ተከትሎ በሲዳማ ሲጧጧፍ የነበረው እስር ጋብ ማለቱ ተገለጸ

የሲዳማ ክልል ጥያቄን ኣንግቦ በተቀጣጠለው ህዝባዊ ንቅናቄ ህዝብን በመንግስት ላይ በማነሳሳት በምል ሃዋሳ ከተማን ጭምሮ በተለያዩ የሲዳማ ወረዳዎች በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ይካሄድ የነበረው ግለሰቦችን የማሰር እንቅስቃሴ ጋብ ብሏል። በኣለፉት ሶስት ሳምንታት ውስጥ ከሃምሳ በላይ የሚሆኑ ግለሰቦች መታሰራቸው የሚታወስ ሲሆን፤ ከታሰሩት ማካከል ካላ ብርሃኑ ሀንካራን ጨምሮ በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ሃዋሳ ከተማ ከምገኘው ፍርድ ቤት የቀረቡ ወደ ኣስር የሚሆኑ ግለሰቦች ቀጠሮ ተሰጥቷቸው ወደ ማረሚያ ቤት ተመልሰዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ኣቶ መለስ ዜናዊን ይተካሉ ተብሎ የሚጠበቁት የኣገሪቱ ምክትም ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኣቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ በሲዳማ የክልል ጥያቄን በተመለከተ በምኖራቸው ኣቋም ላይ የተለያዩ ኣስተያዬቶች እየተሰጡ ነው። ያነጋገርናቸው  ካላ ደመቀ ዳንጋሞ እና ቤላሞ ባሻ   የሃዋሣ ከተማ ነዋሪዎች እንደምሉት ከሆነ፤ ኣቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ከሲዳማ ህዝብ ጋር የኖሩና ሲዳማን ህዝብ ጠንቅቀው የሚያውቁ በመሆናቸው ለክልል ጥያቄው ኣዎንታዊ ምላሽ ልሰጡ ይችላሉ። ይህንን ኣስተያየት የተቃረኑት ካላ ኣስፋ ላላንጎ እና ካላ ናኦራ ቡኤ በበኩላቸው፤ ኣቶ ኃይለማርያም ካለፉት ኣስር ዓመታት ጀምሮ ጸረ ሲዳማ ኣቋም ያላቸው እና ከኣስር ኣመታት በፊት በርካታ ሲዳማዎች በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች እንዲገደሉ ካደረጉት የደቡብ ክልል ባላስልጣናት መካከል ኣንዱ በመሆናቸው የክልል ጥያቄውን በተመለከት የሚኖራቸው ኣቋም ኣዎንታዊ ልሆን ኣይችልም ብለዋል። ክቡራን የብሎጋችን ኣንባቢያን የሲዳማ ክልል ጥያቄ እና የወደፊት እጣ ፋንታ በተመለከተ ያላችሁን ኣስተያየት በሚከተለው ኣድራሻ ላኩልን፦ no

Life after Ethiopia's Meles Zenawi - Inside Story - Al Jazeera English

Life after Ethiopia's Meles Zenawi - Inside Story - Al Jazeera English New

ኢትዮጵያ ከጠቅላይ ሚኒስትር መለስ በኋላ

Image
በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሞት ምክንያት በኢትዮጵያ የሥልጣን ሳይሆን የአመራር ብቃት ክፍተት ሊያጋጥም እንደሚችል አንድ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ጉዳዮች ተንታኝ አስታወቁ ። በአለም አቀፉ የፀጥታ ጉዳዮች ጥናት ተቋም አጥኚ ዶክተር መሐሪ ታደለ ለዶቼቬለ እንደተናገሩት በመለስ አለመኖር አገሪቱ የሥልጣን ክፍተት አያጋጥማትም እስካሁን የመረጋጋት ችግር እልታየባትምም ፣ወደፊት ግን የአመራር ብቃት ክፍተት ሊኖር ይችላል ። በፖለቲካው መስክ የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት ደግሞ ገዥው ፓርቲ የምክክር ና የስምምነት መድረኮችን ማዘጋጀቱ ጠቃሚ ይሆናል ብለዋል ። ላለፊት 21 አመታት ኢትዮጵያን በፕሬዝዳንትነትና በጠቅላይ ሚኒስትርነት ከመሩት ከአቶ መለስ ዜናዊ ህልፈት በኋላ የገዥው ፓርቲ የኢህአዲግ አመራር እንዴት ይቀጥላል ? ኢትዮጵያስ ከመለስ በኋላ ከአለም አቀፉ ማህበረሰብ የምታገኘው ድጋፍና የሚኖራት ተቀባይነት ምን ይሆናል ? መለስስ በምን ይታወሳሉ የሚሉትና የመሳሰሉት ጥያቄዎች ማነጋገራቸውን ቀጥለዋል ። በአለምአቀፍ የፀጥታ ጉዳዮች ጥናት ተቋም ተመራማሪ ዶክተር መሐሪ ታደለ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአመራር ዘመናቸው በኤኮኖሚና ማህበራዊ መስኮች ለኢትዮጵያ አዳዲስ ውጤቶች ማሰገኘታቸው ይጠቅሳሉ ። በፖለቲካው መስክ ግን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይከተሉት የነበረው መርህ ብዙ ችግሮችና ቅሬታዎች ያስከተሉ እንደነበር ዶክተር መሐሪ ገልፀዋል ። ይም ሆኖ ሃገሪቱ መሠረታዊ እንቅስቃሴ ውስጥ እንድትገባ ያደረጉ ጠቅላይ ሚኒስትር ነበሩ ብለዋል ። ከእንግዲህ በኋላስ የሚለው ሌላው ጥያቄአችን ነበር ። ዶክተር መሃሪ እንደሚሉት በተለይ አቶ መለስ ጥሩ አመራር ሰጥተው ውጤት አሳይተዋል ባሉት የኢኮኖሚ መስክ የታዩ ለውጦችን መቀጠል ከባድ ፈተና መሆኑን ይገልፃሉ ። በፖለቲካ መስክ ደግሞ አሁ

ከደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል መንግስት የተሰጠ የሐዘን መግለጫ

የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል መንግስት ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ከድህነትና ኋላቀርነት ለማላቀቅ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ በቅንነትና በታማኝነት አገራቸውን አገልግለው ከፍተኛ የለውጥ ተስፋ ያሳዩትን ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሕልፈተ ህይወት የሰማነው በታላቅ ድንጋጤና መሪር ሐዘን ነው፡፡ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ አምባገነኑን የደርግ ስርዓት ለማስወገድ በተደረገው ትግል በመታገልና በማታገል ለሀገራችን ለውጥ ታላቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ታላቅ መሪ ነበሩ፡፡ እንዲሁም ሀገራችን የህገ መንግስት ባለቤት እንድትሆንና በህገ መንግስቱና በህገ መንግስታዊ ስርዓቱ መሰረት ጠንካራ መንግስት እንዲኖራት ለማድረግ የታገሉ ግንባር ቀደም መሪያችን ነበሩ፡፡ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በሀገራችን ለተመዘገበው እድገት መሰረት የሆኑ ፖሊሲዎችንና ስትራቴጂዎችን ነደፈው ተግባራዊ እንዲደረግ ግንባር ቀደም ሚና የተጫወቱና በነዚህ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች አማካኝነት ለተመዘገበው እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የነበራቸው መሪም ነበሩ፡፡ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ራሳቸውን እንዲያስተዳድሩ፣ የፌዴራል ስርዓት እውን እንዲሆን ላደረጉት ከፍተኛ አስተዋጽኦ፣ ዛሬ የክልላችንና የሀገራችን ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ለተጎናፀፏቸው ራስን በራስ የማስተዳደርና በልማት አስተዋጿቸው ልክ የመጠቀም አቅጣጫ ከፍተኛ አስተዋጽኦ የነበራቸው መሪያችን በመሆናቸው የክልላችን ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች የዝንተ ዓለም ባለውለታ ናቸው፡፡ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በሀገራችን ብቻ ሳይሆን በአፍሪካና በአለም አቀፍ ደረጃ የተለያዩ ችግር ፈቺ ሐሳቦችን በማመንጨትና በማፍለቅ ሀገራችንና አህጉራችን በአለም አቀፍ ደረጃ