Posts

በ5 አመቱ (2002-2007) የእድገትና የትራንስፎርሜሽን እቅድ አቶ ኃ/ማሪያም ደሳለኝ፣ አቶ ሽፈራው ሽጉጤና አቶ አለማየሁ አሰፋ በሲዳማ ህዝብ ላይ ማህበራዊ፤ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ደባ ለመፈጸም ያዘጋጁት ምስጥራዊ እቅድ ተጋለጠ

Image
Top secret /unclassified Dossi / ከውስጥ ኣዋቂ ምንጭ(ሲዳማ ዊኪሊክ)  የ5 አመቱ (2002-2007) ለሲዳማ የታቀደ የእድገትና የትራንስፎርሜሽን እቅድና ውይይትና ውሳኔ  ማስታወሻ፡-  1) የዚህ ዕቅድ ውይይትና ውሳኔ ፋይል በከፍተኛ ሚስጥር የሚጠበቅ ሆኖ ለኔም የደረሰኝ በጣም ቅርብ ከሆነው ጓደኛዬና ከሁሉም በላይ ለሰው ልጅ ማንነትና መብት ከሚቆረቆር ዜጋ ነው፡፡ 2) ውይይቱ የተካሄደው በሶስት የክልሉ ከፍተኛ ባለስልጣኖች ሲሆን እነሱም፡- አቶ ኃ/ማሪያም ደሳለኝ፣ አቶ ሽፈራው ሽጉጤና አቶ አለማየሁ አሰፋ ናቸው፡፡ ቦታው በኃ/ማሪያም ደሳለኝ ቢሮ አ/አበባ ነው፡፡ ውይይቱ የተደረገው ከአራት ወር በፊት ሲሆን ዕቅዱ የተነደፈው በ2002ዓ.ም ሆኖ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ የእቅዱ ውሳኔዎች አንዳንዶቹ ተግባራዊ እየተደረጉ ያሉ ሆኖ የዚህኛው ውይይት ውሳኔ ካለፈው በበለጠ ተግባራዊ ስለሚደረግበት ሁኔታ ነው፡፡ 3) የውይይቱ ውሳኔ ሙሉ ይዘቱ ለሌሎች አምስት ም/ፕረዝዳንቶች ባሉት ብቻ የተገለፀው በአቶ ሽፈራውና በአቶ አለማየሁ አሰፋ ሲሆኑ ሌሎቹ የካብኔ አባላት ግን ሙሉውን ውሳኔ ሳይሆን ለጊዜው ተግባራዊ ለማድረግ የፈለገውን ውሳኔ ብቻ ተራ በተራ ነው፡፡ 4) የትኛው ውሳኔ በምን ጊዜ በአጀንዳነት ተዘጋጅቶ ለታችኛው መዋቅር መውረድ እንዳለበ የሚወሰኑት አቶ ሽራውና አቶ አለማየሁ ናቸው፡፡ 5) አንዳንድ ውሳኔዎች ለታችኛው መዋቅር በተለይም ለሲዳማ ካድሬዎች የማይወርዱ/የማይገለፁ/ እንዳሉ የሚገልፅ ቢሆንም የትኞቹ ውሳኔዎች እንደሆኑ ግን በግልፅ አያስቀምጥም፡፡ 6) ወደ ውይይቱና ወደ ውሳኔው ከመግባታቸው በፊት ሦስቱም እርስ በእርስ ሂስና ግለሂስ የተደራረጉ ሲሆን በኃ/ማሪያም ላይ የቀረበው ሂስ ‘አንተ የራስህ ወገ

በሃዋሳ ከተማ በ60 ሚሊዮን ብር የህግ ታራሚዎችን በሙያ አሰልጥኖ የሚያወጣ ዘመናዊ የማረሚያ ተቋም በመገንባት ላይ ነዉ

Image
  ሃዋሳ ፎቶ ወራንቻ ኔት ሃዋሳ 4/2004 የህግ ታራሚዎችን በተለያዩ ሙያዎች በማሰልጠን፣በእውቀት በማነጽ የክህሎት ባለቤት ለማድረግ 60 ሚሊዮን ብር በሚጠጋ ወጪ ዘመናዊ የማረሚያ ተቋም ግንባታ በመካሄድ ላይ መሆኑን የደቡብ ክልል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር አስታወቀ ። የክልሉ ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ኮሚሽነር አቶ አዳነ ዲንጋሞ ሰሞኑን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት የክልሉ መንግስት በመደበው ገንዘብ የሚካሄደው ግንባታ ታራሚዎች ወደ ህብረተሰቡ ሲቀላቀሉ የተለያዩ ሙያ ባለቤት በመሆን አምራችና ብቁ ዜጋ ሆነዉ እንዲወጡ ለማድረግ የሚያስችል ነው፡፡ በሃዋሳ ከተማ በመገንባት ላይ የሚገኘው ይኽው ዘመናዊ ማዕከላዊ የማረሚያ ተቋም የመመገቢያ አዳራሽ፣የህክምና ክፍል፣የመጀመሪያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ቤተ እንዲሁም የተለያዩ የሙያ ማስልጠኛ ማዕከላት፣ የመዝናኛና የስፖርት ሜዳዎችን ያካተተ መሆኑን አስታዉቀዋል ። የማእከላዊ ማረሚያ ተቋሙ ግንባታ በሚቀጥለው የበጀት አመት አጋማሽ ተጠናቅቆ ለአገልግሎት እንደሚበቃ ኮሚሽነሩ ተናግረዋል፡፡ የማዕከሉ መገንባት ታራሚዎች በቆይታቸው በሚያገኙት ዕውቀት በሀገራችን በመካሄድ ያሉ የሰላም ፣የመልካም አስተዳደርና የልማት ስራዎች ላይ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ የሚያስችላቸዉ መሆኑንም አስታዉቀዋል ። በማዕከሉ የሚገኘዉ የህክምና ተቋም በክልሉ የተለያዩ ወረዳዎች ሪፈር የሚጻፍላቸዉን ህሙማን ተቀብሎ እንደሚያስተናግድ ገልጠዋል ። ከዚሁ በተጨማሪ 86 ሚሊዮን ብር በሚጠጋ ወጪ የወላይታ ሶዶ ፣ የዲላ፣ የሆሳዕናና የሚዛን ተፈሪ ማረሚያ ተቋማት ትምህርት ቤቶች፣ ስልጠና ማዕከልና ሌሎችንም በማካተት በአዲስ መልክ የመገንባት ለሌሎች 18 ማረሚያ ተቋማት የጥገናና የእድሳት ስራ በመከናወ

ኣንዳንድ እውኔታዎች ስለ ታዋቂው ኣትሌት በላይኔ ዴንሳሞ

Image
Belayneh Densamo (born June 28, 1965 in Diramo Afarrara, Sidamo) is a long-distance track and road running athlete from Ethiopia. He held the world record in the marathon for 10 years (1988-1998). This was the third longest span without the record being broken since the event was first organized at the 1896 Olympics. The record was set when he ran 2:06:50 at the 1988 Rotterdam Marathon in the Netherlands. The record was eventually broken by Ronaldo da Costa at the Berlin Marathon in 1998. As of 2009, Densamo lives in the area of Cambridge, Massachusetts. He is no longer active in international competition. ሙሉ የበላይኔን የውድድር ውጤቶችን ለማየት ከፎቶው ላይ ዴብል ክሊክ ኣድርጉ

በባህላዊ ማዕድናት ልማት ዘርፍ የታቀደውን ያህል ምርት አልተገኘም፤ ኣዲሱ እቅድ የሲዳማን ወርቅ ኣምራቾች ይጠቅም ይሁን?

Image
የባህላዊ ማዕድናት ምርትና ግብይትን በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ትናንት በተደረገው ውይይት እንደተመለከተው፤ ከጋምቤላ ክልል ውጭ በሁሉም ክልሎች የባህላዊ ማዕድናት ምርት ከዕቅድ በታች ነው። ከ2001 ዓ.ም ወዲህ የባህላዊ ማዕድናት ምርት ጭማሪ እያሣየ ቢሆንም በ2004 በጀት ዓመት ግን እንደታቀደው አይደለም። በዘርፉ የ2004 በጀት ዓመት አፈፃፀምና የ2005 በጀት ዓመትን ዕቅድ ያቀረቡት በማዕድን ሚኒስቴር የባህላዊ ማዕድናት ምርትና ግብይት ማስተባበሪያ ዳይሬክተር አቶ ታምራት ሞጆ እንደሚናገሩት፤ ከተወሰኑ ክልሎች በስተቀር የባህላዊ ማዕድናት ምርት በአብዛኛዎቹ ክልሎች የመቀነስ ሁኔታ ታይቶበታል። በዘርፉ የምርት መቀዛቀዝ እንደታየና የ2004 በጀት ዓመት አፈፃፀም 63 በመቶ እንደሆነ አመልክተው፤ ከገቢ አንፃር ከዕቅድ በላይ የሆነ አፈፃፀም መመዝገቡን ግን ያመለክታሉ። ለገቢው መጨመር እሴት ተጨምሮላቸው የሚላኩ ምርቶች ማደግና የወርቅ ዋጋ ከጊዜ ወደ ጊዜ መጨመር በአብነት ተነስቷል። እንደ አቶ ታምራት ገለፃ፤ በዘርፉ ችግሮች እያጋጠሙ ሲሆን በተለይም የሚመለከታቸው አካላት በሚፈለገው መንገድና ፍጥነት በቅንጅት አለመሥራት፣ ለዘርፉ የሚሰጠው ትኩረት ማነስ፣ የባለሙያ መፍለስ፣ ፈቃዶችን በአግባቡ አለማስተዳደር ዋና ዋናዎቹ ችግሮች ናቸው። ሕገ ወጥ የማዕድናት ምርት እንዲሁም ወርቅ በባህላዊ መንገድ የሚመረትባቸው አብዛኞቹ አካባቢዎች የመሠረተ ልማት ችግሮች መኖራቸውም ሌሎች የዘርፉ ተግዳሮቶች ናቸው። «በዘርፉ ማኅበራትን ማደራጀት አስቸጋሪ መሆኑን ጠቅሰው፤ ለሮያሊቲ ክፍያ ያለው የግንዛቤ ማነስ ተጨማሪ ችግር ነው» ሲሉም ይናገራሉ። በውይይቱ ተሣታፊ የሆኑ የክልል የማዕድን ቢሮ ተወካዮች በበኩላቸው እንደሚሉት፤ ለዘርፍ ዕድገት ከላይ እስከታች በቅን

የሕገ መንግሥታት ያላቻ ንፅፅርና የኢ-ዘላቂነት ዳንኪራ

በበሪሁ ተወልደ ብርሃን አንድን ነገር ከመጻፌ በፊት ራሴን እንዲህ ብዬ እጠይቃለሁ፡፡ መጻፌ ጥቅም ይኖረው ይሆን? የምጽፈው ነገር ምክንያታዊ ነውን? ይህ ካልሆነ ግን ዝምታን እመርጣለሁ፡፡ ዛሬ ለመጻፍ ስነሳም ለጥያቄዎቼ በቂ ምላሽ ከሰጠሁ በኋላ ነው፡፡ ሪፖርተር ጋዜጣ በሐምሌ 15 ቀን 2004 ዓ.ም. ዕትሙ በአገራችን ዕውቅ ከሆኑ የሕግ ምሁራንና ባለሙያዎች ጋር የጠቅላይ ሚኒስትሩን መታመም በማስታከክ፣ ‹‹ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጊዜያዊ ወይም ቋሚ ሕመም ቢያጋጥመው ማን ተክቶት ይሠራል ለሚለው የሕገ መንግሥቱ አንቀጽ ክፍተት አለበት›› በሚል ርዕስ የቀረበውን ጽሑፍ አንብቤ የተነሳው ጭብጥ፣ አስፈላጊነትና ወቅታዊነት ብዙም ባላምንበትም፣ በተነሱት አንዳንድ ሐሳቦች ላይ ከተነሱት ሕገ መንግሥታዊ መርሆዎችና ድንጋጌዎች ምክንያታዊ እሳቤ (rationale)፣ ይዘት (content)፣ መልእክት (message)፣ ትርጓሜ (interpretation) እና ማብራርያ ምሳሌዎች (illusturation) ረገድ የምስማማባቸውን ትቼ፣ በማልስማማባቸው ሐሳቦች ላይ ይን መጣጥፍ ስጭር፣ በተነሱት ጉዳዮች ላይ ምላሽ ለመስጠትና ለእሰጥ አገባ በር ለመክፈት እንዳልሆነና በሠለጠነው ሐሳብ የማንሸራሸር ውቅያኖስ ላይ ጠበል ጠዲቅ ከመቃመስ አኳያ ብቻና ብቻ እንደሆነ ግንዛቤ እንዲወሰድበት እፈልጋለሁ፡፡ ስለዚህ ሕገ መንግሥትና ሕገ መንግሥታዊነት፣ ሕገ መንግሥት ከሌሎች ሕጎች የሚለይበት መሠረታዊ ባሕርያት፣ የፓርላማ ሥርዓትና የጠቅላይ ሚኒስትርነት ሥልጣን መሠረታዊ መገለጫዎችና ከፕሬዚዳንታዊ ሥርዓት የሚመሳሰሉበትና የሚለያዩበት ሁኔታ፣ የአስቸኳይ ጊዜ ማዕቀፍ፣ ሕገ መንግሥታዊ ክፍተትና የኢፌዲሪ ሕገ መንግሥት በጠቅላይ ሚኒስትሩ አሰያየምና ያንፀባረቀው አቋም፣ እንደ መንደርደርያነት በመመልከት