Posts

የሲዳማ ክልል ጥያቄ የሚመለሰው በኣቶ ሽፈራው በጎ ፍቃድ ሳይሆን ህገ መንግስቱ በሚፈቅደው መሰረት በመሆኑ ጥያቄውን በቀጠይነት ለምመለከቻቸው ከፍተኛ የፈደራል መንግስት ኣካላት እንደሚያቀርቡ የሲዳማ ሽማግሌዎች ኣስታወቁ፤ ኣቶ ሽፈራው ሽጉጤ በበኩላቸው የሲዳማን ክልል ጥያቄ ባለመቀበል ኣቋማቸው እንደሚገፉ ገለጹ

Image
የሲዳማ ሽማግሌዎች በዛሬ እለት በሲዳማ ባህል ኣዳራሽ የከተሙት የሲዳማ ሽማግሌዎች በሲዳማ የክልል ጥያቄ ዙሪያ ከደቡብ ክልል ፕሬዚዳንት ከኣቶ ሽፈራው ሽጉጤ ጋር ሲመክሩ ውለዋል። በስብሰባው ላይ ከኣንድ ወር በፊት በወጣው የማወያያ ጽሁፍ ላይ በሃዋሳ ከተማ ኣስተዳደር ውስጥ በኣንዳንድ መደቦች ላይ ከሲዳማ ተወላጆች ውጪ ለማስቀመጥ እና ከተማዋን ከሌሎች ብሄሮች ጋር ለማስተዳደር በሚያስችሉ ሁኔታዎች ላይ ለመወያያት የማወያያ ጽሁፍ ተዘጋጅቶ ነበር ኣቶ ሽፈራው ሽጉጤ ኣምነዋል። የተዘጋጀው የማወያያ ጽሁፍ በድንገት ከህዝብ እጅ መግባቱ እና የማወያያ ጽሁፉ ይዘትም ለህዝባዊ ንቅናቄ ምክንያት መሆኑን ኣስታውሰው:፤ መንግስትም ይህንን የተያዘው እቅድ መተውን እና በከተማዋ ኣስተዳደር ውስጥ ክፍት በነበሩ ቦታዎችም ላይ የሲዳማ ተወላጆች መሾሙን ተናግረዋል። ኣክለውም  የማወያያ ጽሁፉ በማስቀረት እና ክፍት በነበሩ መደቦች ላይ የሲዳማ ተወላጆችን በመሾም መንግስት ህዝባዊ ንቅናቄውን ለመረጋጋት ጥረት ማድረጉን ጠቁመው፤ ህዝባዊ ንቅናቄ ተባብሶ ለምን ልቀጥል እንደቻሉ ሽማግሌዎቹን ጠይቀዋል። ሽማግሌዎቹን የሲዳማ ህዝባዊ ንቅናቄ የሃዋሳን ከተማ ኣስተዳደር ብቻ የተመለከተ ሳይሆን የክልል ጥያቄን ያነገበ መሆኑን ኣስረድተው፤ የክልል ጥያቄውን ለሚመለከተው ከፍተኛ የመንግስት ኣካል እንዲያቀርቡ ጠይቀዋል። ኣቶ ሽፈራው ሽጉጤ ኣቶ ሽፈራውም ሽማግሌዎቹ ያቀረቡትን የክልል ጥያቄ እንደማይቀበሉ ገልጸው፤ ሲዳማ በደቡብ ክልል ውስጥ መሆኑ የበለጠ የልማት ተጠዋሚ ያደርገዋል የሚለውን እና ሌሎች ነጥቦችን በማንሳት የክልል ጥያቄው እንዲቀር ኣሳስበዋል። የሲዳማ ሽማግሌዎቹም በበኩላቸው ሲዳማ ክልል መሆኑ ለህዝቡ ልያስገኝላቸው የሚችለውን ኢ

ውቧ ሃዋሳ ከተማ የሲዳማ መዲና!

Image
የኣረንጓደዋ እና የንጽህዋ ሃዋሳ ከተማ መንገዶች እና ህንጻዎች፤ የቅርብ ጊዜ ትራክንግ ሾት 

Quotes from Great Sidama Heroes

Aliito Heewano:  “Ille’ya diamaxxeemmo; La’anna shiiyye’e; Ille’ya amaxxummoro, dagganoo ilamara gedensu bushanno.”  English translation:'I do not cover my eyes; kill me while I am watching; If I do cover my eyes, it would be devastation for generations to come'.   Taklu Yota :  "Koo! mannu taaloho!Massangeenna gulufoottohu dirri; Massagoottohu gulufi; massagssiisoottohu massagi". English translation: 'All men are equal! the one who are riding guided horse, dismount; the one who are guiding, get up on it; the one who ordered the guiding, do it yourself '.  

ሃዋሳ የከተማ አውቶብስ ትራንስፖርት አገልግሎት ልትጀምር ነው

Image
ሀዋሳ ፣ ሀምሌ 20፣ 2004 (ኤፍ ቢ ሲ) ሃዋሳ የከተማ አውቶብስ ትራንስፖርት አገልግሎት ልትጀምር ነው። በቅርቡም አራት አውቶብሶች ገብተው ስራ እንደሚጀምሩ ነው የከተማዋ አስተዳደር  ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት  የገለፀው ። አውቶብሶቹ ከከተማዋ ውጭ ለሚገኙ አዋሳኝ ከተሞችም የትራንስፖርት አገልግሎት ይሰጣሉ ። የከተማዋ አስተዳደር እንደሚለው ለነዋሪዎች የትራንስፖርት አማራጭ ከመስጠትም ባለፈ በከተማዋ ቀስ በቀስ ደረጃቸውን በጠበቁ የትራንስፖርት አገልግሎት ለማቅረብ ያስችላል ። አውቶብሶቹን ስራ ለማስጀመር 24 የማቆሚያ ፌርማታዎች ተለይተዋል። በአሁኑ ወቅት በከተማዋ የትራንስፖርት አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ ከ3 ሺህ በላይ የሚበልጡ ተሽከርካሪዎች ሲኖሩ ፥ ከእነዚህ ውስጥ አብዛኛዎቹ ባጃጆች ናቸው። የአስተዳደሩ የትራንስፖርት ፅህፈት ቤት እንደሚለው የአውቶብሶቹ ወደ ከተማዋ መግባት ነዋሪው አማራጭ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲያገኝ ያስችላል ፤ ዘገባው የታደሰ ብዙዓለም ነው።

የአስራ ሁለተኛ ክፍል መሰናዶ ተማሪዎች የፈተና ውጤት ይፋ ሆነ ፤ ለሲዳማ ተማሪዎች መልካም እድል እንመኛለን

አዲስ አበባ፣ ሀምሌ 20፣ 2004 (ኤፍ ቢ ሲ) የአስራ ሁለተኛ ክፍል መሰናዶ ተማሪዎች የፈተና ውጤት ዛሬ ረፋድ ላይ በሀገር አቀፍ ፈተናዎች ድርጅት ድረ ገጽ ይፋ ተደረገ። ፈተናውን የወሰዱ ተማሪዎች ውጤታቸውን በሀገር አቀፍ ፈተናዎች ድርጅት ድረ ገጽ  WWW. nae.gov.et  መመልከት ይችላሉ። በ2004 ዓ.ም ወደ ዪኒቨርሲቲ መግቢያ ሀገር አቀፍ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ቁጥር 156, 997 ነው። የሀገር አቀፍ ፈተናዎች ድርጅት ዋና ዳይሬክተር አቶ አራዓያ ገብረእግዚአብሔር ዛሬ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንዳስታወቁት የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ነጥብ በአስራ አምስት ቀናት ውስጥ ይፋ ይደረጋል።