Posts

የሲዳማ ዳይስፖራ በማወያያ ጽሁፉ ላይ የሰላ ሂስ ኣቀረበ

ሜትሮፖሊታን ከተማችንን እንዴት እንምራው? በሚል የደኢህዴን ስራ ኣስፈጻም ኮሚቴ በተዘጋጀው የማወያያ ጽሁፍ ላይ ከተላያዩ ኣካላት እየቀረበ ያለው ትችት ተፋፉሞ ቀጥሏል፡፡የሲዳማ ዳይስፖራ በማወያያ ጽሁፉ ላይ የሰላ ሂስ ኣቅርቧል። በኣቀረበው ሂስ ላይ የማወያያ ጽሁፉን ከተለያየ ጎን የተመለከተው ሲሆን፤ ከስያሜው ጀምሮ በጽሁፉ ውስጥ የተነሱ እና ትኩረት የተሰጣቸውን ጽንስ ሀሳቦች ገምግመዋል። ''The Sidama leadership that ensured that Hawassa grew faster than any other towns in the country during the past 20 years is regarded as having no political commitment and capacity to deliver these all of the sudden! Another blatant fallacy!''   ከጽሁፍ ተቀንጭቦ የተወሰደ::  የማወያያ ጽሁፉ እና የዳይስፖራውን ሂስ በሚቀጥለው ሊንክ ይመልከቱ። ደኢህዴን በሃዋሳ ከተማ እጣ ፋንታ ላይ በየደረጃው ያሉት ኣመራሮች ለማወያያት ያዘጋጁት ባላ 15 ገጽ የማወያያ ጽሁፍ Ethiopia Regime Manfesto Uprooting Sidama From City

የሜትሮፖሊታን ከተማችንን እንዴት እንምራው? በሚል የደኢህዴን ስራ ኣስፈጻም ኮሚቴ በሃዋሳ ከተማ የወደፊት እጣ ፋንታ ላይ በየደረጃው ካሉት ከሚመለከታቸው ኣመራሮች ጋር ውይይት ለማድረግ ኣዘጋጅቶት በነበረው በለ 15 ገጽ የማወያያ ጽሁፍ ላይ ትችት ቀረበ:: የማወያያ ጽሁፉ የሲዳማ ህዝብ ማህበራዊ፤ኢኮኖሚያዊ እና ባህላዊ እሴቶቹን የሚያንቋሽሽ እና ስራ ኣስፈጻሚ ኮሚቴ ለ ህዝቡ ያለውን ንቀት የሚያሳይ መሆኑ ተገለጸ::

የሲዳማ ምሁራን የማወያያ ጽሁፉን በተመለከተ በተለያዩ ማህበራዊ መረቦች ላይ ያቀረቡት ትችት እንደምያመለክተው፡ በደኢህዴን ስራ ኣስፋጻሚ ኮሚቴ የተዘጋጀው የማወያያ ጽሁፍ የሃዋሳ ከተማ በጥቂት ኣመታት ውስጥ ያሳየችው እድገት በሲዳማ ኣስተዳደር ብቃት መሆኑን የ ሚ ክድ፤ የሲዳማን ህዝብ እንግዳ ተቀባይነትን ከግምት ውስጥ ያላስገባና በጭፍን የሲዳማን ህዝብ የሚያጥላላ ነው ብለዋል :: በማወያያ ጽሁፉ ላይ የቀረበውን ሙሉ ትችት እንደምከተለው ኣቅርበናል :: ሲዳማ ከዘመነ አፄ ምኒልክ እስከ ደኢህዴን/ኢህአዴግ የአፄ ምኒልክ ተዋጊ ኃይል የሲዳማን ህዝብ በአስከፊ ጭቆናና ብዝበዛ ስር ለማስተዳደር ባካሄደው ወረራ በወቅቱ ይጠቀምበት የነበረውን የጦር መሳሪያ ከህዝቡ ስነ-ልቦናዊ ዝግጅት አንጻር የማይጣጣም በመሆኑ የሲዳማን ህዝብ በግፍ እየጨፈጨፈ እስከ ደቡባዊ አገር ድረስ መዝለቁ አልቀረም፡፡ በወቅቱ ያደረሰው ብዝበዛና ጭቆና የህዝባችንን ሰብዓዊ ክብር ያዋረደና ነፃነቱን ያሳጣ በመሆኑ የሲዳማ ህዝብ በቡድንና በተናጥል ባልተደራጀ ሁኔታም ቢሆን ከምኒልክ ወረራ ጀምሮ እስከ አፄ ኃይለስላሴ ውድቀት ድረስ ለማንነቱና ለሰብዓዊ ክብሩ ያደረጋቸው የነፃነት ተጋድሎዎች ለታሪክ የሚዘከሩ ናቸው፡፡ በተለያየ መንገድ ፈርጀ ብዙ የሆኑ የፀረ ነፍጠኛ ወይንም መልከኛ ትግል እስከ ደርግ መንግስት ቀጥሎ የመልከኛ ስርዓት ተወገደ፡፡ እንደማንኛውም ነፃነት ፈላጊና ገባሪ ብሔሮች ሁሉ የሲዳማ ሕዝብ የተቀማውን የመሬት ባለቤትነት መብት አገኘ፡፡ ቀጣይ የማንነትና የዴሞክራሲያዊ መብት ጥያቄዎች ባይመለሱለትም የሲዳማ ሕዝብ ከ70 ዓመታት በፊት ከአባቶቹ እጅ የተነጠቀውን መሬት መልሶ በማግኘት ለአጭር ጊዜም ቢሆን እፎይታ ያገኘ መስሎ ቢታይም ሰው በላው የወቅቱ መንግሥት ግን በር

በሲዳማ ዞን እየተነሳ ባለው ተቃውሞ የመንግስት እጅ አለበት ተባለ

Image
ሰኔ ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የአዋሳ ነዋሪዎች ለኢሳት እንደገለጡት ለዘመናት ተቻችለው የኖሩ ህዝቦች እንዲጋጩ ለማድረግ የመንግስት ባለስልጣናት ሆን ብለው እየሰሩ ነው። ህዝቡ በኑሮ ውድነቱ፣ በመብት አፈናው እና በተለያዩ አስተዳደራዊ ችግሮች እየተማረረ፣ ከዛሬ ነገ ለውጥ ይመጣል እያለ በሚናፍቅበት በዚህ አስቸጋሪና አስፈሪ ወቅት፣ መንግስት የዋሳ ከተማን አስተዳደር እንደገና የህዝብ አጀንዳ አድርጎ በማቅረብ ግጭት እንዲነሳ መጣሩ ነዋሪዎችን አስቆጥቷል። የዞኑ ባለስልጣናት የሚያስወሩት ዘርን ከዘር የሚያጋጭ ወሬ የከተማው ህዝብ የፍርሀትን ካባ እንዲደርብ እንዳደረገው ነዋሪዎች ይገልጣሉ። በዛሬው እለት ዳቶና  መምቦ በተባሉ አካባቢዎች ተማሪዎች ያሰሙትን ተቃውሞ ተከትሎ ዘርፊያ መካሂዱን፣ መኪኖች ታግተው መዋላቸውን ዘጋቢዎቻችን ገልጠዋል። በከተማዋ አሉ ሱቆች ዝርፊያ በመፍራት ተዘግተው መዋላቸውን ለማወቅ ተችሎአል። በዳቶና መምቦ አካባቢዎች የፌደራል ልዩ አድማ በታኝ ፖሊሶች በአስለቃሽ ጭስ ተቃውሞውን ለመቆጣጠር መቻላቸውን ውጥረቱ ግን አሁንም መኖሩን ዘጋቢዎች ገልጠዋል። ግጭቱ  ከአዋሳ ከተማ እጣ ፋንታ አልፎ የዘር ጉዳይ እየሆነ መምጣቱ፣ የከተማውን ህዝብ ለሁለት መክፈሉም እየተነገረ ነው። የሲዳማ አገር ሽማግሌዎች ለዘመናት ተፈቃቅሮ የኖረውን ህዝብ የሚያበጣብጠው መንግስት በመሆኑ ተቃውሞው ሁሉ መንግስት ላይ እንዲሆን ወጣቶችን የማሳመን ስራ እየሰሩ ነው። የሲዳማ ተወላጅ ያለሆኑ የአዋሳ ነዋሪዎች ጥያቄው ከዘር አልፎ አገርአቀፍ አጀንዳ ይዞ ከመጣ ሊቀላቀሉዋቸው ዝግጁ መሆናቸውን እየገለጡ ነው። አንድ ስሙን መግለጥ ያልፈለገ ወጣት ችግሩ እንዲህ በቀላሉ ይፈታል ብሎ እንደማያምን ገልጦ ፣ ተቃውሞውን ወደ ችግር ፈጣሪው መን

ሲኣን የሲዳማ ህዝብ ህገ መንግስታዊ ክልል የመሆን ጥያቄ በኣስቸኳይ እንድመለስ ጠየቀ፤ በሲዳማ ህዝብ ስም እየነገዱ የሲዳማን ማንነት ለመሸጥ የምሯሯጡ ጥቂት ኣድርባዮች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ኣስጠነቀቀ::

New ሲኣን የሲዳማ ህዝብ ህገ መንግስታዊ ክልል የመሆን ጥያቄ በኣስቸኳይ እንድመለስ ጠየቀ፤ በሲዳማ ህዝብ ስም እየነገዱ የሲዳማን ማንነት ለመሸጥ የምሯሯጡ ጥቂት ኣድርባዮች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ኣስጠነቀቀ:: የሲዳማ ኣርነት ንቅናቄ ሲኣን በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ የሲዳማ ህዝብ በህገ መንግስቱ የተሰጡትን የዲሞክራሲያዊ መብቶች ህጉና ደንቡን መሰረት በማድረግ በሰላማዊ መንገድ ስጠይቅ መቆየቱን ኣስታውሶ ከተጠየቁት ጥያቄዎች ኣንዳቸውም ተጨባጭ ምላሽ እንዳላገኙ ኣመልክቷል:: የሲዳማ ህዝብ የጠየቀው ክልል የመሆን ጥያቄ በህገ መንግስት የተደነገጉውን ክልል የመሆን ቅድመ ሁኔታ በተገቢው መልኩ ያሟላ ቢሆንም ገዥው ፓርቲ ለራሱ ኣገዛዝ እንዲመቸው ሲል ጥያቄውን በልማት ሽፋን ሳይመልስ መቆየቱን ጠቅሶ፡ ኣሁንም ቢሆን በድጋሚ የተነሳው የክልል ጥያቄው በኣግባቡ እንዲመለስ ጠይቀዋል:: ኣያይዞም በሲዳማ ህዝብ ስም እየነገዱ የህዝቡን ማንነት ለማሸጥ የምሯሯጡ ኣድርባዮች ከድርጊቻቸው እንዲቆጠቡ ኣስጠንቅቋል:: የጋዜጣዊ መግለጫውን ሙሉ ቃል በሚቀጥላው ሊንክ ይመልከቱ : የሲዳማ ኣርነት ንቅናቄ ሲኣን በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ

ኢሳት ተብሎ የሚጠራው የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን በሲዳማ ዞን ውስጥ በመከሄድ ላይ ያለውን የህዝብ ንቅናቄን በተመለከተ የሚያቀርባቸው ኣንዳንድ ዘገባዎች የህዝባዊ ንቅናቄ ኣላማ ከግምት ውስጥ ያላስገቡና ግጭቶችን የሚያባቡሱ ናቸው በሚል ቅረታ ቀረበ::

New ኢሳት ተብሎ የሚጠራው የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን በሲዳማ ዞን ውስጥ በመከሄድ ላይ ያለውን የህዝብ ንቅናቄን በተመለከተ የሚያቀርባቸው ኣንዳንድ ዘገባዎች የህዝባዊ ንቅናቄ ኣላማ ከግምት ውስጥ ያላስገቡና ግጭቶችን የሚያባቡሱ ናቸው በሚል ቅረታ ቀረበ:: ቅረታ ኣቅራቢዎቹ እንደምሉት ከሆነ ኢሳት ሰሞኑን በተከታታይ በሲዳማ ዞን ውስጥ በመከሄድ ላይ ያለውን ህዝባዊ ንቅናቄውን እንደ ህዝባዊ ኣመጽ ኣድርጎ ማቅረቡ ትክክል ኣይደለም ብለዋል::  የዞኑ ነዋሪዎች ህገ መ ንግስቱ በሚፈቅደው መሰረት በማቅረብ ላይ ያሉትን የክልል ጥያቄ ከህዝባዊ ኣመጽ ጋር ተያያዥነት እንደሌለው ገልጸዋል:: ከዚህም በተጨማሪ በዞኑ ውስጥ ከፍተኛ የሆን የጎሳ ግጭት ልነሳ ይችላል በማለት የሚያቀርበው ዘገባ የሲዳማ ህዝብ ከሌሎች ህዝቦች ጋር ለዘመናት ተቻችሎ ኣብረው የመኖር ባህሉ ላይ ጥላ ሽት እንደመቀባት እና የሲዳማን  ህዝብ ገጽታ እንደማባላሸት ይቆጠራል ብላዋል:: ኢሳት ሌሎች የኣገሪቱ የዜና ኣውታሮች ለመዘጋብ ወኔ ባጡት የሲዳማ ዞን ህዝባዊ ንቅናቄ ላይ ተከታታይ ዘጋባዎችን በማቅረቡ ያላቸውን ኣድናቆት የገለጹት እነኝው ቅረታ ኣቅራቢዎች ፤ ዘጋባዎቹን በ እውኔታ ላይ የተሞረከዙ በማድረግ የሲዳማ ህዝብ የክልል ጥያቄ እንዲደግፍ ጠይቀዋል:: ከቀረቡት ቅረታዎች መካከል ለኣብነት ያህል የሚቀጥለውን ይመልከቱ:   Dear Ethsat Editor, Thank you for your hard work in informing Ethiopian Diaspora and further. The reason of this email is in order.  It's to let you know my utter disappointment after I've watched your purely one-side