Posts

በሲዳማ ዞን ሐዋሣ ዙሪያ ወረዳ አርሶ አደሮች የሐዋሳ ሐይቅንና ጥልቀት የሌላቸው ጉድጓዶችን በመጠቀም ከ800 በላይ ሄክታር መሬት በአነስተኛ መስኖ አልምተው ተጠቃሚ እየሆኑ እንደሚገኙ የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት አስታወቀ:

በሲዳማ ዞን ሐዋሣ ዙሪያ ወረዳ አርሶ አደሮች የሐዋሳ ሐይቅንና ጥልቀት የሌላቸው ጉድጓዶችን በመጠቀም ከ800 በላይ ሄክታር መሬት በአነስተኛ መስኖ አልምተው ተጠቃሚ እየሆኑ እንደሚገኙ የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት አስታወቀ::ተጠቃሚ አርሶ አደሮቹ እንደተናገሩት በአመት 4 ጊዜ የተለያዩ የጓሮ አትክልቶችንና ወቅታዊ ሰብሎችን በማምረት እስከ 1 ሚሊዮን ብር ገቢ ማግኘት ችለዋል:: የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ክፍሌ ሻሾ እንደገለጹት በመስኖው ልማት ከ2ሺ 500 በላይ አርሶ አደሮች ተጠቃሚ ሆነዋል::በመንግሥት ድጋፍ የተገኙትን 20 የውሃ መሣቢያ ሞተሮችን በ1ለ5 ትስስር ለተደራጁ አርሶ አደሮች በማከፋፈል ዓመቱን በሙሉ ዝናብ ሳይጠብቁ በማምረት ተጠቃሚ እየሆኑ እንደሚገኙ አስረድተዋል:: አርሶ አደሮቹ ቲማቲም፣ ጥቅል ጎመን፣ ሽንኩርትና ቃሪያ ከሚያለሙዋቸው ምርቶች ዋና ዋናዎቹ ናቸው ብለዋል::በአሁኑ ጊዜ ማሳ ላይ ከሚገኘው ምርትም ከ1 ሚሊዮን በላይ ኩንታል ይገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅ አቶ ክፍሌ ገልፀዋል ሲል የሲዳማ ዞን የመ/ኮ/ጉ/መምሪያ ዘግቧል :: Back

በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት/ኢጋድ/ አባል ሀገራት አዲስ እቅድ ላይ የሚነጋገር አውደ ጥናት በሀዋሳ ተጀመረ

Image
New አዋሳ, ሚያዝያ 23 ቀን 2004 (ሃዋሳ) - በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት/ኢጋድ/ አባል ሀገራት ተግባራዊ የሚደረገው አዲሱ የግጭት ቅድመ ማስጠንቀቂያና አፋጣኝ ምላሽ ስልት ስትራቴጂክ ዕቅድን ለማዳበር ኢትዮጵያ የበኩሏን አስተዋጾኦ እያበረከተች መሆኗ ተገለጸ፡፡ በስትራቴጅክ ዕቅዱ ላይ ለመምከርና ሀሳብ ለማሰባሰብ የተዘጋጀ አውደ ጥናት ትናንት በሃዋሳ ከተማ ሲጀመር የግብርና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ምትኩ ካሳ እንደገለጹት በአፍሪካ ቀንድ በተለይ በኢጋድ አባል ሀገራት የሚከሰቱ ግጭቶች ለልማት፣ለመልካም አስተዳዳርና ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን ለመገንባት የሚደረገውን ጥረት አሉታዊ ተጽልኖና ጫና እያሳረፉበት እንዳለ ይታወቃል፡፡ የግጭቶች መንስኤ እንደ ሰዎች ፍላጎትና ባህሪ ተለዋዋጭ መሆናቸውን ገልጸው ችግሮቹ በኢትዮጵያና በጎረቤት ሀገር በአርብቶ አደር አካባቢ ለጥሎሽ የሚጠየቀውን ከብት ከሌላ ጎሳ ለማምጣት መሞከር፣ውሃና ግጦሽ ፍለጋ ፣የተመጣጠነ የሀብት ጉድለት የመሳሳሉ ችግሮች መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡ ለኢትዮጵያና ለቀሩትም የኢጋድ አባል ሀገራት ትልቁ ጠላት ድህነት ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው የሚከሰቱ ግጭቶች ከድህነት ጋር የተያያዙ በመሆናቸው ችግሮቹን ከምንጫቸው ለማድረቅ እንደያአካባቢው ተጨባጭ ሁኔታ ህብረተሰቡን ባሳተፈ ሁኔታ አዲስ የጋራ ስትራቴጂክ ዕቅድ እየተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ ቀደም ሲልም ከሌሎች የኢጋድ አባል ሀገራት ጋር በመተባበር የግጭት ቅድመ ማስጠንቀቂያና አፋጣኝ ምላሽ ስልት እንዲቋቋም ግምባር ቀደም ሚና በመጫወት ድንበር ተሻጋሪ የአርብቶ አደር ግጭቶችን በመከላከልና ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ስትንቀሳቀስ መቆየቷን ተናግረዋል፡፡ ላለፉት አምስት አመታት የቆየው ፕሮግራም በቅ

Coffee processing in Sidama, Ethiopia

Image
http://www.firstpost.com/topic/place/vietnam-coffee-processing-in-sidama-ethiopia-video-Z6dCWkYVNpw-270-7.html

በሀዋሣ ዙሪያ ወረዳ የሚገኙ መሠረታዊ ማህበራት ከ9 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል ማስመዝገብ መቻላቸው ተገለፀ::

Image
በሀዋሣ ዙሪያ ወረዳ የሚገኙ መሠረታዊ ማህበራት ከ9 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል ማስመዝገብ መቻላቸው ተገለፀ::የወረዳው የግብይትና ህብረት ስራ ጽህፈት ቤት እንዳለው በ23 ቀበሌያት የተቋቋሙት ማህበራት ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማቱን በማገዝ በመንቀሳቀስ ላይ ናቸው:: የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ጴጥሮስ ማርቆስ ማህበራቱ በሁለገብ መሠረታዊ ህብረት ስራ፣ በወጣት፣ በገንዘብ ቁጠባና ብድር እንዲሁም በወተትና የወተት ተዋፅኦ፣ በኃይድሮ ኤሌክትሪክና ሶላር ማህበራት የተቋቋሙ መሆናቸውን ተናግረዋል::መስኖ፣ ማዕድንና የደን ልማት ቀሪዎቹ ማህበራቱ የተደራጁባቸው መስኮች መሆናቸውን ኃላፊው ጠቁመዋል:: የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ መኮንን ወላንሳ በበኩላቸው ህብረት ስራ ማህበራት የነበሩባቸውን የአመለካከትና ግንዛቤ ችግር ቀርፈው ችግር ፈቺ እየሆኑ መምጣታቸውን መናገራቸውን የወረዳው የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ዘግቧል:: http://www.smm.gov.et/_Text/08MiyaTextN104.html

በሲዳማ ዞን አለታ ወንዶ ወረዳ 16ቱን የጤና ኤክስቴንሽን ፓኬጆች ተግባራዊ ያደረጉ 228 አባወራዎችና እማወራዎች ማስመረቁን የወረዳው ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስታወቀ::

Image
በሲዳማ ዞን አለታ ወንዶ ወረዳ 16ቱን የጤና ኤክስቴንሽን ፓኬጆች ተግባራዊ ያደረጉ 228 አባወራዎችና እማወራዎች ማስመረቁን የወረዳው ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስታወቀ::የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ታደሰ አኔቦ አንዳሉት በጤና ኤክስቴንሽን ኘሮግራም የግልና የአካባቢ ንጽህናን፣ የቤተሰብ ጤና ክብካቤንና የተላላፊ በሽታዎች ቁጥጥር በቤተሰብ ደረጃ እውን እንዲሆን መጠነ ሰፊ ርብርብ እየተደረገ ይገኛል:: ርብርቡን ስኬታማ ለማድረግም በወረዳው የዛሬዎቹን ጨምሮ 38 ሺህ 459 አባወራና እማወራዎች መሰልጠናቸውን ኃላፊው ጠቁመዋል::የዞኑ ጤና መምሪያ መከላከልና ጤና ማጎልበት ኦፊሰር አቶ ኢማላ ላሚቻ በበኩላቸው መንግስት የህብረተሰቡን የጤና አገልግሎት ተጠቃሚነትና ተደራሽነት ለማረጋገጥ የነደፈውን የጤና ፖሊሲ ስኬታማ ማድረግ ከተመራቂዎች የሚጠበቅ ተግባር ነው ማለታቸውን የወረዳው የመንግስት ኮሚኒኬሽን ዘግቧል:: http://www.smm.gov.et/_Text/08MiyaTextN304.html