የሃዋሳ ዩኒቨርስቲ በሲዳምኛ ቋንቋ በመጀመሪያ ድግሪ የትምህርት ፕሮግራም ሊከፍት ነው፡፡
ሃዋሳ ነሃሴ 6/2004/በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የብሄር ብሄረሰቦችን ቋንቋ ለትምህርትና ለምርምር ስራ ለማዋል እየሰራ መሆኑን የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት አስታወቁ፡፡ የሃዋሳ ዩኒቨርስቲ የሲዳምኛን ቋንቋን ለመጀመሪያ ጊዜ በድግሪ የትምህርት ፕሮግራም ለመጀመር መዘጋጀቱም ተመልክቷል፡፡ የሲዳምኛን ቋንቋን በመጀመሪያ ድግሪ ደረጃ ለማስተማር የተቀረጸው የስርዓተ ትምህርት ለመገምገምና የማዳበሪያ ሀሰብ ለማከል ትናንት በሀዋሳ ከተማ የምክከር መድረክ ተካሂዷል ። የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ዮሴፍ ማሞ በምክክር መድረኩ ላይ እንደገለጹት የሀገራችን ብሄር ብሄረሰቦችን ማንነትን፣ ባህል፣ ታሪክና ወግ የሚጠናበትና የሚታወቅበት መንገድ ለማመቻቸት ራሱን የቻለ የቋንቋ ጥናት ትምህርት አስፈላጊ ነዉ ። ዩኒቨርስቲው በደቡብ ክልል ከ54 በላይ ብሄር ብሄረሰቦች ማዕከል በሆነችው ሀዋሳ ከተማ እንደመገኘቱ አሁን በሲዳምኛ ቋንቋ በድግሪ ደረጃ የትምህርት ፕሮግራሙን ለመክፈት የተደረገዉ ዝግጅት ተጠናቆ ከያዝነው ክረምት ጀምሮ ወደ ተግባርይሸጋግራል ብለዋል ። በሲዳምኛ ቋንቋ በድግሪ ደረጃ የሚጀምረዉ የትምህርት ፕሮግራም በማስፋፈት ወደፊት የሌሎችንም ብሄር ብሄረሰቦችን ቋንቋ በተመሳሳይ የመማሪያና የምርምር ስራ ለማዋል እቅድ መኖሩንም ዶክተር ዮሴፍ አስታውቀዋል፡፡ በተለያዩ ቋንቋዎች የመጀመሪያ ድግሪ ፕሮግራም መከፈት የብሄር ብሄረሰቦችን ባህላዊ እሴት ከማሳደግ ባለፈ ሌሎች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎች እንዳሉት ተናግረዋል ፡፡ የዩኒቨርስቲው የሶሻል ሳይንስና ሂዩማኒቲ ኮሌጅ ዲን ዶክተር ንጉሴ መሸሻ በበኩላቸው የሲዳምኛን ቋንቋን በድግሪ ፕሮግራም በሀገር አቀፍ ደረጃ የመጀመሪያ መሆኑን ገልጠዋል ። በዚህ የትምህርት ደረጃ መኖሩ የብሄርሰቦች አፍ መፍቻ ቋ