Posts

ኤጀንሲው የብሄራዊ ፈተና ጥያቄዎችን ማስቀመጥ የሚያስችል የጥያቄ ባንክ ሊያዘጋጅ ነው

Image
አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 8 ፣ 2006 ( ኤፍ.ቢ.ሲ. ) የሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና የፈተናዎች ኤጀንሲ የብሄራዊ ፈተና ጥያቄዎችን አስቀድሞ በማዘጋጀት ለማስቀመጥ የሚያስችል የጥያቄ ባንክ ሊያዘጋጅ ነው። የኤጀንሲው ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ዘሪሁን ዱሬሳ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደተናገሩት ፤ የጥያቄ ባንኩ ኤጀንሲው በማንኛውም ጊዜ በየትኛውም የትምህረት አይነት በርካታ ዝግጁ የሆኑ ጥያቄዎች እንዲኖሩት የሚያስችለው ነው። ይህ ደግሞ በየአመቱ ለጥያቄዎች ዝግጅት የሚያስፈልገውን የሰው ሃይልና ወጪ ለመቆጠብ ያስችላል። በተጨማሪም በማንኛውም ጊዜ ብሄራዊ ፈተናን መስጠት ቢያስፈልግ ኤጀንሲው ዝግጁ ሆኖ እንዲገኝ ያግዘዋል። የጥያቄ ባንኩ በስራ ላይ ሲውልም በአንድ የትምህርት አይነት እስከ 5 ሺህ የሚደርሱ ተቀማጭ ጥያቄዎች ኤጀንሲው እንዲኖሩት ያስችለዋል ነው ያሉት አቶ ዘሪሁን ። በርካታ ያደጉ ሀገራት አሰራሩን ለረጅም አመታት የተጠቀሙበት ሲሆን በኢትዮጵያም ተግባራዊ ለማድረግ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ መሆናቸውንም ነው የገለጹት።

ሲዳማ ቡና ኢትዮጵያ ቡናን ኣሽነፈ

Image
አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 9 ፣ 2006 (ኤፍ.ቢ.ሲ.) ትናንት በተደረጉ 20ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ  ጨዋታዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ለመጀመሪያ ጊዜ አቻ ሲለያይ ደደቢት አሸንፏል። ቅዱስ ጊዮርጊስ 28 ነጥብ ይዞ በሶስተኝነት ደረጃ ላይ ከሚገኘው መከላከያ ጋር ያደረገው ጨዋታ 0 ለ 0 በሆነ ውጤት ነው የተጠናቀቀው። ይህን ተከትሎም ቅዱስ ጊዮርጊስ ስድስት የፕሪሜየር ሊግ ጨዋታዎች እየቀሩት ሻምፒዮን መሆን የሚያስችለውን ውጤት ማሳካት አልቻለም። በመጀመሪያው ግማሽ ቅዱስ ጊዮርጊስ የተሻለ የግብ ሙከራ ማድረግ ችሏል። በሌላ በኩል  ደደቢት  በዘጠኝ ነጥብ በሊጉ የመጨረሻ ደረጃ ላይ የሚገኘው ኢትዮጵያ መድንን 2 ለ 0 አሸንፏል። በሌሎች ጨዋታዎች ሙገር ሲሚንቶ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1 ለ 1 ፣ ሀረር ከተማ ከወላይታ ዲቻ 0 ለ 0 ሲለያዩ  ሲዳማ ቡና ኢትዮጵያ ቡናን 1 ለ 0 እንዲሁም አርባምንጭ ከነማ መብራት ሃይልን 3 ለ 2 አሸንፈዋል። በክልል ትናንት  ጎንደር ላይ ሀዋሳ ከነማን ያስተናገደው ዳሽን ቢራ በ37ኛ ደቂቃ በጣለው ከባድ ዝናብ ጨዋታው ተቋርጦ የነበረ ሲሆን ዛሬ ጨዋታው ከቆመበት ቀጥሎ  0 ለ 0 በሆነ ውጤት ተጠናቋል።

በjazz ሙዝቃ ስሙ እየገነነ ያለው የሃዋሳው ልጅ፦ ዮሃንስ ጦና

Image
A native of Ethiopia and now a veteran of the local jazz and gospel scene, bassist Yohannes Tona is featured on the next Jazz at Studio Z ("Made in Abyssinia") on May 10th. His trio (Geoff LeCrone on guitar, Shai Hayo on percussion) will present an open, free workshop at 6 pm, followed by the concert ($10 admission) at 7 pm, both in the Studio Z performance space on the second floor of the Northwestern Building in St. Paul's Lowertown. Yohannes Tona  grew up in Awassa in southern Ethiopia, the son of a church organist (father) and vocalist (mother). Studying guitar and then bass in his homeland, he attended Yared, Ethiopia’s lone music school, at sixteen. Yohannes moved on to music studies in the capitol city of Addis, then emigrated in the late 1990s to the U.S. to study at the Berklee College of Music. A few yeas later he was recruited to serve as music director for the Ethiopian Church in Minneapolis. Here he has played with the Grammy-nominated Excelsior Choir ,

በኣሜሪካን ኣልቪን ኣልለይ የዳንስ ትያቴር ተወዳጅነትን እያገኘ ያለው Awassa Astrige/Ostrich ጀማሪ ማነው?

Image
በALVIN AILEY AMERICAN DANCE THEATER ከጊዜ ወደ ጊዜ ተወዳጅነትን እየተጎናጸፈ ያለው ኣዋሳ ኦስትሪች የኣዋሳ ሰጎን የዳንስ ትያቲር ማነው? ጥቂት ሰለ ትያቲሩ ባለቤት ከታች ያንቡ፦ Awassa Astrige/Ostrich (1932)  (Company Premiere – 2014)  Choreography by Asadata Dafora  Recreated by Charles Moore  Restaged by Ella Thompson-Moore  Music by Carl Riley  Costumes by Catti  Lighting Design by Craig Miller  Sierra Leone-born choreographer Asadata Dafora blended his vision of a traditional African dance with Western staging  in Awassa Astrige/Ostrich. This groundbreaking 1932 solo, set to Carl Riley’s score of African drumming and flute,  was one of the first modern dance compositions to fuse African movements with Western staging. With arms flapping like  wings, torso rippling and head held high, a warrior is transformed into the proud, powerful ostrich — the king of birds.  “After the audience buzz died down and the lights dimmed, you heard the slow beat of an African drum for Asadata  Dafora’s Awassa Astrige/Ostrich

የባህል ስፖርቶች ውድድር ነገ በሃዋሳ ይጀመራል፤ መልካም እድል ለሲዴ ተወዳዳሪዎች!

Image
ፎቶ ከ https://www.google.com.pe/url?sa=i&rct=j&q=&esrc=s&source=images&cd=&cad=rja&uact=8&docid=BrtdZFEjwpXJaM&tbnid=T_rvmxNsoecT6M:&ved=0CAQQjB0&url=http%3A%2F%2Fwww.skyscrapercity.com%2Fshowthread.php%3Ft%3D849248%26page%3D4&ei=CGh3U-fqB-irsQTVpICIAg&bvm=bv.66917471,d.aWw&psig=AFQjCNGDgRaNwr-ojorHu46ItlwzfrDbIw&ust=1400420733937651 አዲስ አበባ ግንቦት 9/2006 12ኛው የመላው ኢትዮጵያ የባህል ስፖርቶች ውድድርና ፌስቲቫል ነገ በሃዋሳ ይጀመራል። የኢትዮጵያ የባህል ስፖርት ፌዴሬሽን እንዳስታወቀው ውድድሩ ከነገ ግንቦት 10 ቀን ጀምሮ እስከ ግንቦት 20 ቀን 2006 ዓም ድረስ ይካሄዳል። የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ ከበደ ደስታ እንደተናገሩት በውድድሩ አዲስ አበባና ድሬዳዋን ጨምሮ ሁሉም ክልሎች በዘጠኝ የውድድር አይነቶች ይሳተፋሉ። የባህል ስፖርት ውድድሩ አርሶና አርብቶ አደሩን ጨምሮ በርካታ የህብረተሰብ ከፍል የሚሳተፍበት ይሆናል። ዝግጅቱ በተሳካ ሁኔታ ተጀምሮ እንዲፈጸም ፌዴሬሽኑ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ማድረጉን ፕሬዝዳንቱ ገልጸዋል። ለ10 ቀናት በሚቆየው በዚህ ውድድርና ፌስቲቫል ላይ ከአንድ ሺህ በላይ ስፖርተኞች ይሳተፋሉ። በየክልሎቹ የሚገኙ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች የባህል፣ የቋንቋና የታሪክ ልውውጥ እንደሚያደርጉም ይጠበቃል። የደቡብ ክልል ስፖርት ኮሚሽነር አቶ መዘረዲን ሁሴን በበኩላቸው በሀዋሳ በሚካሄደው የባህል ስፖርቶች ውድ