Posts

የሲዳማ ፓርቲዎች ህብረት ለነጻነት እና ፍትህ (USPFJ)፤ የራሷ እያረረባት የሰው ታማስላለች!

Image
የሲዳማ ፓርቲዎች ህብረት ለነጻነት እና ፍትህ የሰሞኑ ጋዜጣዊ መግለጫ በኣንባቢያ ዘንድ ክርክር ጫረ የተባበሩት የሲዳማ ፓርቲዎች ለነጻነት እና ፍትህ በምጻረ _ ቃል (USPFJ) ሰሞኑን በኢትዮጵያ ውስጥ በኦሮሞ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ላይ በኣገሪቱ የጸጥታ ኃይሎች የተወሰደውን የኃይል እርምጃ በመቃወም ጋዜጣዊ መግለጫ ስጥቷል። በመግለጫውም ለበርካታዎች ሞት እና ኣካል ጉዳት ምክንያት የሆነውን የመንግስት እርምጃ ኮንኗል። ይህንን የድርጅቱን መግለጫ የወራንቻ ኢፎርሜሽን ኔትዎርክ ከጋዳ ድህረገጽ ላይ በማግኘት ለኣንባቢያኑ ያደረሰ ሲሆን፤ የህብረቱን ጋዜጣዊ መግለጫ ተከትሎ የተለያዩ ሰዎች ኣስተያየት በመስጠት ላይ ናቸው። በርካታ ኣንባቢያን ለወራንቻ ኢንፎርሜሽን ኔትዎርክ በጻፏቸው መልዕክቶች እንዳመለከቱት፤ የተባበሩት የሲዳማ ፓርቲዎች ህብረት ለነጻነት እና ፍትህ፤ በበርካታ ሲዳማውያንን እና የሰብኣዊ መብት ተከራካሪ ድርጅቶች የተወገዘውን፦ የኢትዮጵያ የጸጥታ ኃይሎች በቅርቡ በሃዋሳ ከተማ የኣላሙራ እና ታቦር ከፍተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሲዳማ ተወላጅ ተማሪዎች ላይ የወሰዱትን የኃይል ጥቃት ካለማውገዙ በላይ በጥቃቱ ልጆቻቸው ለተጎዱባቸው ቤተሰቦች ኣጋርነቱን ኣለመግለጹን እንዳዛዘናቸው ገልጸዋል። ከኣስተያየት ስጪዎቹ መሃከል፦ ስሙን T H በማለት የጠራው እና የዩቨርሲቲ መምህር መሆኑን የገለጸው ኣስተያየት ሲጪ እንዳለው፤ ህብረቱ ምንም እንኳን እታገልለታለው ከሚለው ህዝብ ጋር የግንባር ለግንባር ግንኙነት የሌለው ብሆንም ባለፉት ኣመታት በሲዳማ ውስጥ ያለውን የፖለቲካ እና ስብኣዊ መብት ጥስቶችን በማጋለጥ ከፍተኛ ሚና መጫወቱን ኣስተውሰዋል። ኣክለውም ህብረቱ በቅርቡ በኦሮሞ ተማሪዎች ላይ በመንግስት የተወሰደውን የኃይል እር

በአዲስ አበባ ዙሪያ ገበሬዎች የሚፈናቀሉት ያለ በቂ ዝግጅት ነው ተባለ፤ ተመሳሳይ እድል ለገጠማቸው የሃዋሳ ዙሪያ ገበሬዎችስ ምን ታስቦል?

Image
የመሬት ወረራ መስመር ሰሜን፦ዳቶ ኦዳሄ ሰሞኑን ኣዲስ ኣድማስ ጋዜጣ እንዳስነበበው በኣዲስ ኣበባ ዙሪያ ኣርሶ ኣደሮች ያለ በቂ ዝግጅት በተለያዩ  ምክንያቶች ከመሬት ይዞታቸው የሚፈናቀሉ ሲሆን፤ ተፈናቃዮቹም ለተለያዩ ችግሮች በመጋለጥ ላይ መሆናቸውን ኣትቷል። በተመሳሳይም ልክ እንደ ኣዲስ ኣበባ ዙሪያ ገበሬዎች የሃዋሳ ዙሪያ ኣርሶ ኣደሮችም ለላፉት 20 ኣመታት ተመሳሳይ ከመሬት ይዞታቸው በተለያዩ ምክንያቶች የመፈናቀል እድል ገጥሞቸዋል። የመሬት ወረራ መስመር ምስራቅ፦ ጫፌ ( ከሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጀርባ ) እነዚሁ ተፈናቃዮች በከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ችግር ውስጥ ከመግባታቸው ባሻገር የኣገር ሽክም በመሆን ላይ ናቸው። መንግስት ይህን መሰል ያለ በቂ ዝግጅት የምደረግ የኣርሶ ኣደር የማፈናቀል ተግባራ ለመግታት ምን እያደረገ ነው? ለማንኛውም ስለ ሃዋሳ ዙሪያ ተፈናቃይ ኣርሶ ኣደሮች በሌላ ጊዜ እንመለስበታለን፤ ለኣሁኑ ግን ስለ ኣዲስ ኣበባ ዙሪያ ገበሬዎች ከታች ያንቡ፦ የመሬት ወረራ መስመር ደቡብ፦ ሎቄ ከግማሽ ሚሊዮን እስከ 2 ሚሊዮን ብር ካሣ የተከፈላቸው ገበሬዎች አሉ በተከፈላቸው ካሣ ንድግ ጀምረው የተሳካላቸው ጥቂቶች ናቸው          “ቦታው ለሪል እስቴትና ለልማት ይፈለጋል ተብለን የእርሻ መሬታችንና የመኖሪያ ቦታችን በመንግስት ከተወሰደብን አራት አመታት ሞላን” ይላሉ - በሰበታ አዋስ ወረዳ እያረሱ ይኖሩ እንደነበር የገለፁ አርሶአደሮች፡፡ ለእርሻ መሬት እንደየስፋቱ ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ ካሳ የተከፈላቸው ገበሬዎች መኖራቸው አይካድም፡፡ ለመኖሪያ ቤትም 24 ሺ ብር ድረስ ካሳ እንደተከፈላቸውና ቤት መስሪያ ቦታ እንደሚሰጥም ቃል ተገብቶላቸው እንደነበር የተፈናቀሉ ገበሬዎች ያስታውሳሉ፡፡ “ከዛሬ ነገ ቦታ ተሰጥቶን ባለችን ብ

The Indiscriminate Killings of Oromo University Students and Other Civilians by Ethiopian Security Forces is Deplorable!

By United Sidama Parties for Freedom and Justice (USPFJ) May 7, 2014 It has been confirmed that the Ethiopian regime’s security forces have indiscriminately massacred over 50 unarmed Oromo University students who were all peacefully demonstrating against the plan of the regime to uproot Oromo peasants from the outskirts of Finfine/Addis Ababa. The casualties were said to have included children of age 6 and the elderly who were marching against the proposed plan. Over 250 Oromo youth and other civilians were seriously injured during the shootings which is said to be continuing sporadically as we speak. More than 2000 Oromo University students and other members of the Oromo nation were unlawfully detained. There is also allegations of torture of those detained. All Universities throughout Oromia were targeted and being encircled by the regime’s killing squad, the infamous ‘Agi’azi’ special force. The massacre began on 29th of April 2014 when Oromo University students peacefully e

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ እየተገነባ ያለው ዘመናዊ ስታዲየም ዩኒቨርሲቲውን የሚያስተዋውቅና የማህበረሰብ አገልግሎትን የሚያጠናክር ማዕከል መሆኑ ተገለጸ

Image
Photo from H.University website: Edited by Worancha Information Network በሀዋሳ ዪኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ፤ በአንድ ጣሪያ ስር ሁሉን-አቀፍ አገልግሎት ሊሰጥ በሚችል መልኩ እየተገነባ ያለው ስታዲየም፤ ተማሪዎች  በዙሪያው   ባሉ መዝናኛ ማዕከላት ተጠቅመው የሚዝናኑበትና ትምህርታቸውንም  ሊያጠኑ  የሚችሉበት ማዕከል መሆኑን የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ቢዝነስና ዴቭሎኘመንት ምክትል ኘሬዚዳንት ኘ/ር ንጋቱ ረጋሳ ገለፁ፡፡   የስታዲየሙ መገንባት ዩኒቨርሲቲው ከሁለት ዓመታት ወዲህ ለስፖርቱ ዕድገት የሰጠው ትኩረት ማሳያ ነው ያሉት ኘ/ር ንጋቱ፤ በከተማው የሚደረጉ ትላልቅ ዝግጅቶችን በማስተናገድ ረገድ ምቹ አማራጭ ሊሆን እንደሚችልና ጎን ለጎንም ዩኒቨርሲቲው የውስጥ ገቢውን ለማሳደግና የአከባቢውን ማህበረሰብ ለማገልገል የሚያመርታቸውን ምርቶች የሚያቀርብባቸው ሱቆች በስታዲየሙ ዲዛይን ውስጥ መካተታቸው ማዕከሉ ለየት ያለ ኮምኘሌክስ ያደረርገዋል ብለዋል፡፡   በስፖርት ሳይንስ የተካኑ ባለሙያዎችን በማፍራት ለሀገሪቱ ስፖርት እድገት በትጋት እየሰራ ላለው ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ፤ ትልቅ ግብዓት እንደሚሆን የታመነበት ይህ ዘመናዊ የስፖርት ማዘውተሪያ ኮምኘሌክስ፤ ለአከባቢው የስፖርት ቡድኖችም የመወዳደሪያና የልምምድ አማራጭ በመሆን ዩኒቨርሲቲው የማህብረሰብ አገልግሎትን የበለጠ እንደሚያጠናክር የሚጠበቅ ሲሆን፤ እስካሁን ድረስ ለግንባታው 140 ሚሊዮን ብር ወጪ መደረጉን ኘ/ር ንጋቱ አስረድተዋል፡፡ የዩኒቨርሲቲው ግንባታ ኘሮጀክት ጽ/ቤት ሥራ አስክያጅ የሆኑት አቶ ደንበሹ ነኤሬ በበኩላቸው የስታዲየሙን ግንባታ በማስመልከት በሰጡት ገለጻ¿ ዩኒቨርሲቲው በ2002 ዓ.ም የመንግስት ከፍተኛ ዩኒቨርሲቲዎችን ስፖርት ውድድር ለማዘጋጀት አምስት ሺህ

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት 2ኛውን የኦፕን ዶር(Open-Door) ቀን አከበረ

Image
የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት እና የደቡብ ብ/ብ/ህ/ክ/መ ንግድ ኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ቢሮ በጋር በመሆን ሁለተኛውን የኦፕን ዶር ቀን በደመቀ ሁኔታ ሚያዝያ 14/2006 ዓ.ም አከበሩ፡፡ "የዩኒቨርሲቲ ኢንዱስትሪ ትስስር ለህዳሴያችን" በሚል መሪ ቃል በተከበረው በዓል ላይ የፕሬዚዳንት ጽ/ቤትን በመወከል ዶ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ የመክፈቻ ንግግር አድረገዋል፡፡ እሳቸው እንዳሉት ኦፕን ዶር በሀገራችን ብዙም ያተለመደ ነገር ግን የተለያዩ የምርምርና የቴክሎጂ ውጤቶችን የምናስተዋውቅበት ዘርፈ ብዙ ጠቃሜታዎች አሉት ብለዋል፡፡ ዶ/ር ፍቅሬ አክለውም ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በቴክኖሎጂው ዘርፍ እምርታና ለውጥ ለማምጣት ዩኒቨርሲቲው ከአውሮፓ ከካናዳ እና አሜሪካ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ተባብሮ እየሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡ ዶ/ር ሞልቶት ዘውዴ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር በበኩላቸው እንዳተናገሩት መድረኩ በዩኒቨርሲቲውና እና በኢንስዲስትሪው መካከል ከፍተኛ ትስስር የሚፈጠርበትና ኢንስቲትዩቱ የሚሰራቸውን ስራዎች የምናስተዋውቅበት ነው ብለዋል፡፡ ዶ/ር ሞልቶት አክለው ይህ ቀን እንዲከበር በገንዘብና በተለያዩ ቁሳቁሶች ዩኒቨርሲቲውን የደገፈው የክልሉ ንግድ ኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ቢሮን አመስግነዋል፡፡ ለግማሽ ቀን በዩኒቨርሲቲው የስልጠና ማዕከል በተካሄደው መድረክ በኢንስቲትዩቱ ስር የሚገኙ የትምርት ክፍሎችና ት/ት ቤቶች እያከናወኗቸው ያሉትን ተግባርና እንቅስቃሴ አስተዋውቀዋል፡፡ በመቀጠልም የዩኒቨርሲቲ ኢንዱስትሪ ትስስርን ለማጠናከር የሚያስችል የመወያያ ሰነድ በዶ/ር ሞልቶት ዘውዴ ቀርቧል፡፡ ውይይቱንም የደቡብ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መ ምክትል ርዕሰ መስተዳደርና የክልሉ ንግድ ኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ቢሮ ኃላፊ የሆኑት