Posts

የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በ415 ሚሊዮን ብር ወጪ የሚያካሄደው የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ህንጻ ግንባታ በመፋጠን ላይ ነዉ

Image
ሃዋሳ ነሐሴ 8/2005 የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ከመንግስት በተመደበለት 415 ሚሊዮን ብር ወጪ የሚያካሄደው የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ፕሮጀክት ህንጻ ግንባታ በመፋጠን ላይ መሆኑን ገለጸ፡፡ ዩኒቨርሰቲው በ2006 የሚያስጀምራቸው ግንባታዎች ጨምሮ ከ2 ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ ሌሎች በርካታ ፕሮጀክቶች እንደሚያካሂድም ተመልክቷል፡፡ በዩኒቨርስቲው የኮንስትራክሽንና ሜንቴናንስ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ደንበሹ ኒኤሬ ሰሞኑን እንደገለጹት ግንባታ በ2004 የተጀመረው የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቱ ህንጻ የመጀመሪያው ምዕራፍ ግንበታ 164 ሚሊዮን ብር የሚፈጅ ነው ። በመገንባት ላየ ያለዉ ህንጻ በርካታ የመማሪያ ክፍሎች፣ የሌክቸር አዳራሽ፣ ቤተሙከራ፣ ቢሮዎች፣ የተማሪዎች መዝናኛዎችን የያዘ መሆኑን አስታዉቀዋል ። በሁለተኛው ምዕራፍ 251 ሚሊዮን ብር የተመደበለት የተማሪዎች ማደሪያና መስተንግዶ፣ የመመገቢያ አዳራሽ፣ የቴክኖሎጂ ላብራቶሪ ጨምሮ ለሌሎች ግንባታዎች እንደሚካሄዱ አስረድተዋል፡፡ በዩኒቨርስቲው ዋና ግቢ የሚገነባዉ ህንጻ የአካል ጉዳተኞች መወጣጫና መመላለሻዎችን ከግምት የሚያስገባ ሲሆን ከአጠቃላይ ግንባታዉ እስከአሁን ከ30 በመቶ በላይ መከናወኑን ጠቁመዋል፡፡ የፕሮጀክቱ ግንባታ በ2007 የስራ ዘመን ተጠናቆ ለአገልግሎት ሲበቃ በመደበኛነት ብቻ 15ሺህ ተማሪዎችን ተቀብሎ የማስተማር አቅም እንደሚኖረው ገልጸዋል፡፡ የኢንስቲትዩቱ መገንባት በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ሀገሪቱ የምትፈልጋቸውን የተማረ የሰው ሃይል በብዛትና በጥራት በማፍራት በተለይ በእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ መሰረት በየአመቱ የሚቀበላቸውን ተማሪዎች 70 በመቶ የሳይንስናቴክኖሎጂ ቀሪው 30 በመቶ ደግሞ የማህበራዊ ሳይንስ ግብ በማሳካት ከፍተኛ አስተዋጾኦ እንዳለው አቶ ደንበሹ አስረድተዋል፡፡ በዩኒቨርስቲው

ሃዋሳ እና የጠቅላይ ሚኒስትሩ ሹመት ከወሰንሰገድ ገ/ኪዳን (ጋዜጠኛ)

Image
ወቅቱ ፦ከኣንድ ኣመት በፊት እንደመነሻ “አዳራሽ ተቀምጣ ስታበላ ሥጋ ስታጠጣ ጠጅ ስዕል ትመስላለች የምኒሊክ ልጅ” እንዲህ ሆነ፡- ዕለተ እሁድ መስከረም 27 ቀን 2005 ዓ.ም ረፋዱ ላይ ድንገት ብድግ ብዬ ወደ ሃዋሳ መረሽኩ፡፡ የሁለት ቅን እና ትንታግ ወጣቶች (መስከረም እና ፍፁም) ደግነት ነው ወደ ሃዋሣ ያንደረደረኝ፡፡ የእንዳልክና የፀሃይም ደግነት የጉድ ነው፡፡ እነሆ ሃዋሳን ለሁለተኛ ጊዜ ረገጥኳት፡፡ ድንቅ ከተማ ናት፡፡ አውራጎዳናዎቿ የተወለወሉ ይመስላሉ፡፡ አንድ ወጥ የሆነ መልክና ስፋት አላቸው፡፡ እንደእኔ ዓይነቱን አልፎሂያጅ መንገደኛ “ሊያምታቱ” ይችላሉ፡፡ አቀያየሳቸውም አነጣጠፋቸውም ፍፁም ተመሳሳይ ስለሆነ ወደሌላ ቦታ መሄድ ያሰበ ሰው ተጉዞ ተጉዞ ራሱን እዚያው የተነሳበት ቦታ ሊያገኘው ይችላል፡፡ ስለዚህ ከከተማዋ አንድ ጥግ ወደሌላ ጥግ መሄድ የፈለገ ሰው፣ ጉዞ ከመጀመሩ በፊት ቆም ብሎ እንደአሸን እየፈሉ ካሉት ትልልቅ ሕንፃዎች መሃል አንዱን በምልክትነት   Posted on Ethiopiansemay.blogspot.com   ሃዋሳ እና የጠቅላይ ሚኒስትሩ ሹመት ከወሰንሰገድ ገ/ኪዳን (ጋዜጠኛ) እንደመነሻ “አዳራሽ ተቀምጣ ስታበላ ሥጋ ስታጠጣ ጠጅ ስዕል ትመስላለች የምኒሊክ ልጅ” እንዲህ ሆነ፡- ዕለተ እሁድ መስከረም 27 ቀን 2005 ዓ.ም ረፋዱ ላይ ድንገት ብድግ ብዬ ወደ ሃዋሳ መረሽኩ፡፡ የሁለት ቅን እና ትንታግ ወጣቶች (መስከረም እና ፍፁም) ደግነት ነው ወደ ሃዋሣ ያንደረደረኝ፡፡ የእንዳልክና የፀሃይም ደግነት የጉድ ነው፡፡ እነሆ ሃዋሳን ለሁለተኛ ጊዜ ረገጥኳት፡፡ ድንቅ ከተማ ናት፡፡ አውራጎዳናዎቿ የተወለወሉ ይመስላሉ፡፡ አንድ ወጥ የሆነ መልክና ስፋት አላቸው፡፡ እንደ

‘Takers’ and ‘Givers’ of Human Rights?

By Mosissa Gamtessa* |  Ilma Orma Currently, there is a fundamental issue concerning ‘Oromo first’ or ‘Ethiopia first’ based on the assertion of the Oromo political analyst Jawar Mohammed as an ‘Oromo first.’ I am a person who always feel angry about the lives of my people, like any other Oromo, but I have never participated on any dialogue or struggle yet. Now, the denial of Abyssinians about the very obvious human rights and facts about Ethiopia has awakened me, and from now on, I assure you, I will give myself for the Oromo cause.  I am an Oromo, and my assertion is even different from that of Jawar; I do not know even whether I am an Ethiopian or not. My assertion is not just offensive, but based on real facts. Basically, God created me as an Oromo and I speak Afan Oromo; I am brought up under an Oromo culture descended down to me through many generations. I have been fed with what  Waaqa  blessed Oromia and much more that attaches me firmly to my Oromo Nation, next to my very

ፊቼ ጫምባላላ በዓልን በዩኔስኮ ቅርስነት ለማስመዝገብ የሚረዳ ጥናት ተጠናቀቀ

Image
-    ሐቻምና ዲዛይኑ የተጠናቀቀው የደቡብ ባህል ማዕከል ግንባታ እስካሁን አልተጀመረም ከደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦች አንዱ የሆነው የሲዳማ ብሔር የዘመን መለወጫ (ፊቼ) በዓል በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት ሳይንስና ባህል ድርጀት (ዩኔስኮ) በዓለም ቅርስነት እንዲመዘገብ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑ ተመለከተ፡፡ የሲዳማ ብሔር ባህልና ማንነት መገለጫ የሆነው የፊቼ በዓል የዓመቱ አዋቂዎች (አያንቶ) በሚወስኑት ቀንና ወር የሚውል ሲሆን፣ የዘንድሮ ዘመን መለወጫ ሐምሌ 29 ቀን 2005 ዓ.ም. ድምቀት ተከብሯል፡፡  በዋዜማው በርችት ሕብረ ቀለማት ተጀምሮ በዕለቱ ከጧት ጀምሮ በባህላዊ መሰብሰቢያ ሥፍራው (ጉዱማሌ ፓርክ) የክልሉና የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች፣ የብሔሩ ተወላጆች፣ ቱሪስቶችና የክብር እንግዶች በተገኙበት በተለያዩ ዝግጅቶች ተከብሯል፡፡ ክብረ በዓሉ በዓለም አቀፍ ቅርስነት እንዲመዘገብ የሚያስችል ጥናት ተጠናቅቆ በሚቀጥለው ዓመት ለዩኔስኮ እንደሚቀርብ የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ገልጿል፡፡ ስለዘንድሮው ፊቼ በዓልና በዓለም ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተደረገ ስለሚገኘው እንቅስቃሴ የሲዳማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ በየዓመቱ እንደሚደረገው በዓሉ ከዘመን መለወጫና በማግስቱ ጫምባላላ አዋቂዎች፣ ወጣት ሴቶችና ወንዶች በልዩ ጭፈራ (ቄጠላ) ታጅቦ እንደሚቀጥል ይናገራሉ፡፡ በየዓመቱ የፊቼ በዓል ዕለትና ወሩ መለያያትን በተመለከተም ‹‹የሲዳማ ጊዜ አቆጣጠር ከጨረቃ ሥርዓት ጋር የተገኘና ከዋክብትና ጨረቃን በመመልከትም የሚተነትኑ አዋቂዎች (በአካባቢው አጠራር አያንቶ) የሚወስን በመሆኑ ነው›› ሲሉ ይገልጻሉ፡፡ የሲዳማ ዘመን መለወጫ (ፊቼ) ከጥንት ጀምሮ ሊከበር የመጣና የራሱ የሆኑ ባህላዊ እሴቶች ያሉት በመሆኑ በዓለም

በሲዳማ ዞን ከ24 ሺህ ሄክታር የሚበልጥ መሬት በመስኖ እየለማ ነው

Image
አዋሳ ነሐሴ 6/2005 በደቡብ ክልል ሲዳማ ዞን በያዝነው በጋ ወራት በመስኖ ከለማ መሬት ከአራት ሚልዮን ኩንታል የሚበልጥ የፍራፍሬ ፣ጓሮ አትክልት፣ስራ ስርና የቋሚ ሰብል ምርት መገኘቱን የዞኑ ግብርና መምሪያ ገለጸ፡፡ በመምሪያው የግብርና ልማት እቅድ የስራ ሂደት ኦፊሰር አቶ ደርቤ በትራ ሰሞኑን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት ምርቱ የተሰበሰበው በሁለት ዙር በበጋው በመስኖ ከለማ 24 ሺህ 550 ሄክታር መሬት ላይ ነው፡፡ በየአካባቢው ምንጭ በማጎልበት፣ አነስተኛ የእጅ ጉድጓዶች በመቆፈር፣ በባህላዊ መንገድ ወንዝ በመጥለፍና በቤተሰብ ደረጃ የኩሬ ውሃ በማሰባሰብ የልማቱ ስራ መከናወኑን ገልጸው በልማቱ ከ530 ሺህ የሚበልጡ አርሶ አደሮች ተሳትፈዋል ብለዋል፡፡ የመስኖ ልማቱ ካለፈው ዓመት በ13ሺህ ሄክታር፣በምርት በሶስት ሚልዮን ኩንታል ብልጫ እንዳለው ጠቁመው በዞኑ አብዛኛው አርሶ አደር ቀደም ሲል የዝናብ ወቅትን ጠብቆ በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ የሚያመርት በመሆኑ መስኖ ልማት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ቁልፍ አማራጭ እየሆነ መምጣቱን ገልጸዋል፡፡ በመስኖ ልማትና ግብአት አጠቃቀም ላይ ለአርሶ አደሮቹ ስልጠና መስጠቱን ገልጸው በልማት ቡድንና በአንድ ለአምስት ተደራጅተው በመስራት በርካታ አርሶ አደሮች ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ የቦርቻ ወረዳ አርሶ አደሮች እንደገለጹት በአከባቢያቸው የሚገኘውን ወንዝ በመጥለፍ ምርጥ ዘርና ማዳበሪያ መጠቀም ከጀመሩ ወዲህ ኑሮአቸው እየተለወጠ ከመምጣቱ ባሻገር ሞዴል አርሶ አደር በመሆን ለሽልማት መብቃታቸውን ገልጸዋል፡፡ http://www.ena.gov.et/Story.aspx?ID=10754&K=1