Posts

በሃወሳ ከተማ ከ34 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ በመገንባት ላይ ያለው የማረሚያ ተቋም ግንባታ ከ90 በላይ ተጠናቀቀ

አዋሳ ሐምሌ 19/2005 የደቡብ ክልል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር በሃዋሳ ከተማ ከ34 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ በመገንባት ላይ ያለው ዘመናዊ የማረሚያ ተቋም ግንባታ ከ90 በመቶ በላይ መጠናቀቁን ገለጸ፡፡ በአስተዳደሩ ማረምና ማነፅ የስራ ሂደት ባለቤት ኮማንደር ኑሪ ሺሾሬ እንደገለጹት የህንጻው መገንባት የህግ ታራሚዎችን በተለያዩ ሙያዎች በማሰልጠን በማረምና በማነፅ የዕውቀትና የክህሎት ባለቤት እንዲሆኑ ለማድረግ ጠቀሜታው የጎላ ነው፡፡ የክልሉ መንግስት በመደበው ገንዘብ የሚካሄደው ግንባታ ታራሚዎች ወደ ህብረተሰቡ ሲቀላቀሉ የተለያዩ ሙያ ባለቤት በመሆን አምራችና ብቁ ዜጋ ሆነው እንዲወጡ ለማድረግ የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡ ማዕከላዊ የማረሚያ ተቋሙ የመመገቢያ አዳራሽ፣የህክምና ክፍል፣የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ቤተመፃሕፍት፣የተለያዩ የሙያ ማስልጠኛ ማዕከል፣ መዝናኛና የስፖርት ሜዳዎችን ያካተተ ሲሆን በሚቀጥለው የበጀት ዓመት አጋማሽ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚበቃ ተናግረዋል፡፡ የማዕከሉ መገንባት ታራሚዎች በቆይታቸው በሚያገኙት ዕውቀት በሀገሪቱ በመካሄድ ያሉ የሰላም ፣የመልካም አስተዳደርና የልማት ስራዎች ላይ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ያስችላቸዋል፡፡ ማዕከሉ በክልሉ ለሚገኙ 22 የማረሚያ ተቋማት የሚያገለግል በመሆኑ በህመም ምክንያት ሪፈር የሚፃፍላቸውን ህሙማን ተቀብሎ እንደሚያስተናግድም ገልጸዋል፡፡ እንዲሁም ከ57 ሚሊዮን ብር በሚበጥ ወጪ በወላይታ ሶዶ፣ በዲላና በሆሳዕና የማረሚያ ተቋማት፣ ትምህርት ቤቶች፣ ስልጠና ማዕከልና ሌሎችንም በማካተት በአዲስ መልክ የመገንባት ስራዎች በመከናወን ላይ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡ በሚዛን አማንና በበንሳ በተመሳሳይ አዲስ የማረሚያ ተቋማት ግንባታ ለማስጀመር የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁንም ኮ

በሲዳማ ዞን ከ30 ሺህ የሚበልጡ አንቀሳቃሾች ተደራጅተው ወደ ስራ ገቡ

ሃዋሳ ሐምሌ 18/2005 በደቡብ ክልል ሲዳማ ዞን በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ከ30 ሺህ የሚበልጡ አንቀሳቃሾችን በማደራጀት ወደ ስራ እንዲገቡ መደረጉን የዞኑ ንግድና ኢንዱስትሪ መምሪያ ገለጸ፡፡ ለአንቀሳቃሾቹ ከ12 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ብድር መሰራጨቱ ተገልጿል፡፡ በመምሪያው የኢንተርፕራይዝ ልማት ዋና የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ደበበ ተገኝ ትናንት ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት የኢንዱስትሪ ልማት መሰረት የሆነውን የአነስተኛና ጥቃቅን መስኮችን የመደገፍና የማብቃት ስራዎች ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ይገኛል፡፡ ባለፉት አሰራ ሁለት ወራት 30 ሺህ 673 አንቀሳቃሾችን በተለያየ ማህበራት በማደራጀት ወደ ስራ እንዲገቡ መደረጉንና ከነዚህም መካከል 8 ሺህ የሚሆኑት ሴቶች ናቸው ፡፡ መምሪያው አንቀሳቃሾቹ ጥራት ያለውን ምርት አምርተው በገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማስቻል በየደረጃው የክህሎትና የቴክኖሎጂ ድጋፍን ጨምሮ ሌሎች የአቅም ግንባታ ስራዎችን በዞኑ ከሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማትና ከሌሎች የባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡ በዚህም አዲስ ወደ ስራ የገቡትን ጨምሮ ከ40 ሺህ በላይ አንቀሳቃሾች ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡ አንቀሳቃሾቹ በማኑፋክቸሪንግ፣ በኮንስትራክሽን፣ በከተማ ግብርና፣ በቀበሌ ተደራሽ መንገድ ግንባታና በሌሎች ዕድገት ተኮር የስራ ዘርፎች ተደራጅተው ወደ ስራ መግባታቸውን ገልፀዋል፡፡ በመምሪያው የድጋፍ ማዕቀፎች አፈፃፀምና ክትትል ዋና የስራ ባለቤት ወይዘሮ ሐረገወይን ኃይለሚካኤል በበኩላቸው በዘርፉ ቀደም ብሎ የሚገኙትንና በአዲስ መልክ ተደራጅተው ወደ ስራ የገቡ አንቀሳቃሾች ስራቸውን ለመጀመርና ለማስፋፋት ከ12 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ብድር እንዲያገኙ መደረጉን አስረድተዋል፡፡ የማምረቻና

በሀዋሳ ከተማ 25 ኪሎ ሜትር የድንጋይ ንጣፍ መንገድ ተሰራ

አዋሳ ሐምሌ 18/2005 በሀዋሳ ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት ከ66ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ 25 ኪሎ ሜትር መንገድ በጌጠኛ ድንጋይ ንጣፍ መሰራቱን የከተማው ማዘጋጃ ቤት ገለጸ፡፡ የማዘጋጃ ቤቱ የመሰረተ ልማት ማስፋፊያ ፕሮጀክት አስተባበሪ አቶ መብራቴ መለሰ ትናንት ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በበጀት አመቱ መግቢያ ላይ የተጀመረው የድንጋይ ንጣፍ መንገዱ ግንባታ በእቅዱ መሰረት በአሁኑ ወቅት ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ለአገልገሎት በቅቷል፡፡ በከተማው አሰተዳደር በጀት የተገነባው የድንጋይ ንጣፉ መንገድ ስራ ሰባት ሜትር ስፋት አለው ብለዋል፡፡ ለእግረኛና ተሽከርካሪ የሚያገልግለው በከተማው ስምንት ክፍለ ከተሞች የተገነባ በመሆኑ በዋጋ ደረጃ ከአስፓልት አንጻር ርካሽና ለረጅም አመታት አገልግሎት እንደሚሰጥ ቢበላሽ በቀላሉ መጠገን የሚቻል መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ስራው ሰልጠነው በተደራጁ 148 ድንጋይ ጠራቢና አንጣፊ ማህበር ከስድስት ሺህ ለሚበልጡ ወጣቶችና ሴቶች የስራ ዕድል መፍጠሩን ገልጸው እያንዳንዱ ማህበራት በየቀኑ እስከ 20 ሌሎች ሰዎችን በመቅጠር ተጠቃሚ ማድረጋቸውን ተናግረዋል፡፡ በከተማው የአሁኑን ሳይጨምር ቀደም ብሎ የተሰራ 55 ኪሎ ሜትር የድንጋይ ንጣፍ መንገድ እንዳለ ተገልጿል፡፡ በሌላ በኩል 17 ኪሎ ሜትር የጠጠር መንገድ ደረጃውን ወደጠበቀ አስፓልት ለማሳደግ በ46 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በግል ተቋራጭ እየተካሄደ እንደሚገኝ ያስረዱት አቶ መብራቴ ይሄው መንገዱ ከነባሩ ቴሌ እሰከ አዴቬንቲስት ቤተክርስቲያን፣ ከመናሃሪያ ዋንዛ ወልደአማኑኤል ዱባለ አደባባይና ከአላሙራ ትምህርት ቤት ወደ ሞኖፓል አቋርጦ የሚያልፍ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ከመንገዱ ስራ እስካሁን ግማሽ ያህሉ መከናወኑንና እሰከ መጪው መስከረም 2006 ተጠናቆ ለአገልገሎት ይበቃል ብለዋ

ሲዳማን ጨምሮ ከደቡብ ክልል ዘንድሮ ከ83 ሺህ 100 ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ቀረበ

ሃዋሳ ሐምሌ 16/2005 በደቡብ ክልል በተጠናቀቀው የበጀት አመት 83 ሺህ 140 ቶን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡን የክልሉ ግብይትና ህብረት ስራ ቢሮ ገለጸ፡፡ በቢሮው የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች የስራ ሂደት ባለቤት አቶ መላኩ እንዳለ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት ቡናው የቀረበው በክልሉ ቡና አምራች ከሆኑ የተለያዩ ዞኖች በሚገኙ 380 የህብረት ስራ ማህበራትና ከ330 በሚበልጡ የግል ባለሃብቶች እንዲሁም የቡና ተክል ልማት ድርጅት አማካኝነት ነው፡፡ በዘመኑ ለማዕከላዊ ገበያ ገበያ ከቀረበው ከዚሁ ቡና ውሰጥ 42 ሺህ 189 ቶን የታጠበና ቀሪው 40 ሺህ 951 ቶን ደግሞ ያልታጠበ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ በስራው ላይም 394 የቡና ማዘጋጃ ኢንዱስትሪዎች ተሳትፈዋል፡፡ ክንውኑ የእቅዱን 68 በመቶ መሸፉኑንና ከአምናው ተመሳሳይ ጊዜ ጋር ሲነጻጸር ብልጫ እንዳለው ጠቁመዋል፡፡ ከዕቅዱ ሊያንስ የቻለው ህገ ወጥ የቡና ግብይትና ዝውውር መበራካት እንዲሁም የአለም ገበያ ዋጋ መቀነስና መዋዥቅ ጋር ተያይዞ ቡና አምራቹ ገበሬና አቅራቢው ወደፊት ዋጋው ይጨምራል በሚል በክምችት መያዙ አቶ መላኩ በምክንያትነት ከጠቀሱት ውስጥ ይገኙበታል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ከክልል እስከ ቀበሌ በየደረጃው የተቋቋመው የቡና ጥራትና ንግድ ቁጥጥር አሰተባባሪ ግብረ ሀይል በማጠናከር ህገ ወጥ ንግድ እንዲቆም ለማድረግ በዘመኑ በተካሄደው እንቅሰቃሴ ጀንፈል፣ መርቡሽ፣ እሸት ቡና ጨምሮ ከ21 ሺህ 700 ኩንታል በላይ ቡና ከህገ ወጦች ተይዞ ከ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ በህጋዊ መንገድ በመሸጥ ለመንግስት ገቢ መሆኑን የስራ ሂደቱ ባለቤቱ ጨምረው ገልጸዋል፡፡

በኢትዮጵያ ገቢዎችና ግምሩክ ባለስልጣን የሀዋሳ ቅርንጫፍ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ከ62 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው የኮንትሮባንድ እቃ ያዘ

Image
ሃዋሳ ሐምሌ 16/2005 በኢትዮጵያ ገቢዎችና ግምሩክ ባለስልጣን የሀዋሳ ቅርንጫፍ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ከ62 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው የኮንትሮባንድ ዕቃ መያዙን አስታወቀ። የቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ያሬድ ፈቃደ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በአራት መቆጣጠሪያ ጣቢያዎች የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ክምችት ይገኝባቸዋል ተብሎ በተጠረጠሩ ከተሞች በተደረገ ፍተሻ 62 ሚሊዮን 400 ሺህ 986 ብር ግምት ያላቸው የተለያዩ አዳዲስና ልባሽ ጨርቆች፣ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች፣ መድሀኒቶችና ሌሎች የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ተይዘዋል። ከተያዙት የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ውስጥ አዳዲስ አልባሳት፣ አሮጌ ልባሽ ጨርቅና ጫማ፣ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች፣ ዘይትና ሌሎች ምግብ ነክ ምርቶች፣ መድሀኒቶች፣ ትምባሆና የትንባሆ ውጤቶች ከፍተኛውን መጠን የያዙ መሆናቸውን አቶ ያሬድ ገልጸዋል። በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት በህገወጥ መንገድ ወደ ሀገር ውስጥ ሲገባ የተያዘው የኮንትሮባንድ ዕቃ መጠን በገንዘብ ሲገመት ከ10 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ብልጫ ያለው የተለያዩ ልባሽና አዳዲስ ጨርቆች መድሀኒቶችና የመዋቢያና የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች መያዛቸውንና ኮንትሮባንድ የመያዝ አቅም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር እድገት ማሳየቱን ተናግረዋል። የኮንትሮባንድ ወንጀልን ለመቆጣጠር በደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የሚመራ ጥምር ኮሚቴ በክልል ደረጃና በክልሉ በሚገኙ አምስት ዞኖችና በምዕራብ አርሲ ዞንና በባሌ ዞን ደረጃ የፀረ ኮንትሮባንድ ጥምር ኮሚቴ ከተዋቀረ ወዲህ የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴ መዳከሙን ገልጸዋል። በግማሽ ዓመቱ ኮንትሮባንድን በተመለከተ ለጽህፈት ቤቱ ከደረሱ ጥቆማዎች ውስጥ አብዛኞቹ ለውጤት መብቃታቸውንና በጥቆማዎቹ መሰረት በተሽከርካሪና በጋማ ከብት ተጭነው ወደ ሀ