የደቡብ ክልል ምክር ቤት ሶስተኛ ዓመት አራተኛ ዙር ስድስተኛ መደበኛ ጉባኤ በሃዋሳ ከተማ እየተካሄደ ነዉ
ሃዋሳ የካቲት 12/2005 በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል በዘንድሮ ግማሽ በጀት ዓመት በየዘርፉ የተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤት የተመዘገበባቸው መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አስታወቁ ። የክልሉ ምክር ቤት ሶስተኛ ዓመት አራተኛ ዙር ስድስተኛ መደበኛ ጉባኤ በሃዋሳ ከተማ እየተካሄደ ነዉ ። ርዕሰ መስተዳድሩ አቶ ሽፈራው ሽጉጤ የክልሉን የግማሽ በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ለምክር ቤቱ ባቀረቡበት ወቅት ካለፈዉ ዓመት ክንውን በየስራ ዘርፉ ምርጥ ተሞክሮዎችን በመውሰድና በማስፋት እስትራተጂ በመጠቀም ውጤታማ ተግባራት ተከናወነዋል ። በመንግስትና በህብረተሰቡ የተሟላ ተሳትፎ የኪራይ ሰብሳቢነትን ችግሮች ለመቅረፍ በሚያሰችል መልኩ በገጠርና በከተማ የተለያዩ ተግባራትን በማከናወን ለውጥ ማምጣት የተቻለ መሆኑን አስታዉቀዋል ። ባለፉት ስድስት ወራት በግብርና ልማት፣ በመንገድ ግንባታና በቀበሌ ተደራሽ መንገድ ስራዎች የገጠር ቀበሌዎችን ዕርስ በዕርስና ከዋና መንገድ ጋር በማገናኘት 705 ኪሎ ሜትር መንገድ ተገንብቶ መጠናቀቁን አርሶና አርብቶ አደሩ ምርቱን ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆኑን አመልክተዋል ። መንገዶቹ በሚገነቡባቸው አካባቢዎች በማህበር ለተደራጁና በጉልበት ሰራ ለተሰማሩ ከ106 ሺህ በላይ ሰዎች የስራ ዕድል መፈጠሩን ጠቁመው ከ668 ሺህ በላይ ነዋሪዎች ለመንገዱ ግንባታ ከ65 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ነጻ የጉልበት አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን ገልጸዋል። የትምህርት ጥራት ፍትሀዊነትና ተደራሽነት በማረጋገጥ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሰ ህጻናት ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ ለማስቻል እንዲሁም በቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት በሚሰጡ ስልጠናዎች ጥራትና ተፈላጊነት ዙሪያ የታቀዱ ተግባራት መከናወናቸውን ጠቁመዋል። በህዝብ ንቅናቄ የታጀበው