Posts

በኢትዮጵያ የከተሞች በዓል ላይ የሃዋሳ ከተማ ተሳትፎ

Image
ከተሞች ተሞክሯቸውን እየተለዋወጡ ናቸው   ዜና ሐተታ አዳማ እንግዶቿን ማስተናገድ ከጀመረች ቀናትን አስቆጥራለች። ማዕዷን እያቋደሰች የምትገኘዋ አዳማ ገፅታዋን ለማስተዋወቅ የአራተኛው የከተሞች ሣምንት ኤግዚቢሽን ተሣታፊ ነች። ለሰባት ተከታታይ ቀናት ለሕዝብ ክፍት ሆኖ የቆየው ኤግዚቢሽን 136 ያህል ከተሞች ወደ አዳማ ያመጣቸውን መገለጫዎቻቸውን በድንኳን በድንኳን ሆነው ራሳቸውን እያስተዋወቁ ናቸው። የአዳማና ዙሪያዋ ከተሞች በርካታ ነዋሪዎች ኢግዜቢሽኑን ይጐበኛሉ። ነዋሪዎቹ አዳማ በዘንድሮው የከተሞች ውድድር አንደኛ እንደምትወጣ ይገልፃሉ። የከተማዋን ገፅታ በኤግዚቢሽኑ እያስጎበኙ የሚገኙ አካላትም ይህንኑ ያጠናክራሉ። አቶ ዘላለም አስራት የአዳማ ከተማን ገፅታ ለማሳየት በተዘጋጀው ድንኳን ውስጥ ስለቀረቡት የተለያዩ ዝግጅቶች ሲያብራሩ «የአዳማ ከተማን ማስተዋወቅ ያስፈለገው ከከተሞች ሁሉ በመሪነት ቦታ ላይ እንድትቀመጥ ታስቦ ነው» ይላሉ። እንደ አቶ ዘላለም ማብራሪያ፤ የአዳማ ከተማ ከ63 ሺ በላይ አባላትን ያቀፉ ከ4ሺ 73 በላይ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች አሏት። ከ280 ኪሎ ሜትር በላይ መንገዷ በአስፋልትና በኮብልስቶን ተሸፍኗል። ከ10 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል የሚያንቀሳቀሱ ከ700 በላይ ባለሀብቶች ይገኙባታል። አዳማ በቀን 45 ሺ የሚሆኑ ሕዝብ ገብቶ የሚወጣበት 7ሺ ያህል ሰዎች ደግሞ የሚያድሩባት ናት። 8ሺና ከዛ በላይ እንግዶችን ሊያስተናግዱ የሚችሉ የተለያዩ የስብሰባ ማዕከላት ያሏት ስትሆን። ይህም ከተማዋን የኮንፈረንስ ከተማ አሰኝቷታል። ለኢንዱስትሪ፣ ለአግሮ ፕሮሰሲንግ፣ ለሪልስቴት፣ ለጤና፣ ለትምህርትና ለተለያዩ ዘርፎች የሚውል 128ነጥብ 70 ሔክታር መሬት ለልማት ማዘጋጀቷንም አቶ ዘላለም ይጠቁማሉ።  የ

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ ከተሞች የህዳሴ ጉዞ በትክክለኛ አቅጣጫ ላይ እንደሚገኝ ገለፁ

Image
“ከተሞች የኢንዱስትሪያሊስቶች መፍለቂያ ማዕከል በመሆን የመለስን ራዕይ ያሳካሉ” በሚል መርህ በአዳማ ሲካሄድ የቆየው 4ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ሳምንት ተጠናቋል፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የትምህርት ሚኒስትሩ አቶ ደመቀ መኮንን በዓሉ በከተሞች መካከል የልምድ ልውውጥ ለማድረግ የሚያስችል እና ጠንካሮችን በማበረታታት በዘርፉ የተያዘውን እቅድ ለማሳካት ንቅናቄ መፍጠር የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡ የከተሞች የህዳሴ ጉዞ በትክክለኛ አቅጣጫ ላይ ይገኛል ያሉት አቶ ደመቀ በማደግ ላዩ ያሉ ከተሞችን ወደ ላቀ የልማት ደረጃ ለማሸጋገር ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሊረባረቡ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ በገጠር እየተመዘገበ ያለው የልማት ውጤት በከተሞች እየታየ ላለው መጠነ ሰፊ ለውጥ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቷል ብለዋል፡፡ ከተሞችንና ገጠሮችን አስተሳስሮ መሄድ ቀጣይ የመንግስት አቅጣጫ መሆኑንም ነው አቶ ደመቀ የተናገሩት፡፡ በ4ኛው የከተሞች ሳምንት ለሰባት ቀናት በቆየው ኤግዚቢሽን ላይ በተለያዩ የከተማ ልማት መስኮች ያከናወኗቸውን ተግባራት እና እራሳቸውን በማስተዋወቅ ከየምድባቸው ላቅ ያለ አፈፃፃም ያስመዘገቡ ከተሞች ተሸልመዋል፡፡ በተለይም በስድስት ቁልፍ የከተማ ልማት ስራዎች የላቀ አፈፃፀም ያስመዘገቡ ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮችም በ4ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ሳምንት ተሸላሚ ሆነዋል፡፡ በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ስራዎች የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልል፣ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የትግራይ ክልል ከአንድ እስከ ሶስተኛ ያለውን ደረጃ ሲይዙ በመሬት ልማትና ማኔጅመንት ስራዎች ደግሞ የትግራይ ክልል አንደኛ፣ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ሁለተኛ እና የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ አሸናፊ ሆነዋል፡፡

የሲዳማ ሕዝቦች አርነት ንቅናቄን ጨምሮ የዘንድሮ ምርጫ ተቃዋሚ ፓርቲዎችንና ምርጫ ቦርድን ማወዛገብ ጀመረ

በታምሩ ጽጌ በሚያዝያ ወር 2005 ዓ.ም. የሚደረገው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤትና የአካባቢ ምርጫ ከወዲሁ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድንና የፖለቲካ ፓርቲዎችን ማወዛገብ ጀመረ፡፡ ቦርዱ ጥቅምት 15 ቀን 2005 ዓ.ም. “የምርጫ ሰሌዳ የምክክር መድረክ” በሚል በአዳማ ከተማ በተደረገው ውይይት፣ በወቅቱ ከተሳተፉት 66 የፖለቲካ ፓርቲዎች ከግማሽ በላይ የሚሆኑት፣ ቦርዱ ካዘጋጀው የመወያያ ርዕሰ ጉዳይ ውጭ የተለያዩ ጥያቄዎችን ማንሳታቸውንና ምላሽ ማጣታቸውን ተከትሎ አለመግባባት ተፈጥሯል፡፡  ቦርዱ ከምርጫ ሰሌዳው በኋላ በሚወጡ የምርጫ የማስፈጸሚያ ደንቦችና መመርያዎችን ረቂቅ አዘጋጅቶ ፓርቲዎቹን ለማወያየት በጠራው የውይይት መድረክ ላይ፣ 41 የሚሆኑ የፖለቲካ ፓርቲዎች የተስማሙበትንና መስተካከል እንዳለበት ያመኑበትን ጥያቄ ማቅረባቸውን፣ በ34 ፓርቲዎች የተወከለውና ሰባት አባላት ያሉት ጊዜያዊ ኮሚቴ ጥቅምት 30 ቀን 2005 ዓ.ም. አስታውቋል፡፡  “በምርጫ ሰሌዳ ዙርያ ከመወያየታችን በፊት የአገሪቱ የፖለቲካ ምኅዳር መጥበብና የምርጫ ውድድር ሜዳው የተስተካከለ አለመሆን፣ ቀደም ብሎ የተደረጉ ምርጫዎች በአፈጻጸም ችግሮች የተተበተቡ መሆቸውን፣ በየደረጃው ያሉ የምርጫ ቦርድ አመራርና አስፈጻሚዎች ተዓማኒነትና ተቀባይነት ላይ ቅድሚያ ሰጥተን ብንወያይ ይገባል፤” የሚል ጥያቄ ከኢሕአዴግና አጋር የፖለቲካ ድርጅቶች ውጭ ያሉት 41 የፖለቲካ ፓርቲ ድርጅቶች ጥያቄ ማንሳታቸውን ኮሚቴው አስታውሷል፡፡  አንድነት ለፍትሕና ለዴሞክራሲ ፓርቲ፣ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት፣ ሰማያዊ ፓርቲ፣ የጌዴኦ ሕዝቦች ንቅናቄ፣ የከንባታ ሕዝቦች ኮንግረንስ፣ የሲዳማ ሕዝቦች አርነት ንቅናቄን ጨምሮ 34 የፖለቲካ ፓርቲዎች ከላይ ያነሷቸው ጥያቄዎች

በሲዳማ ዞን 25 የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ ይካሄዳል

Image
አዋሳ ህዳር 6/2005 በሲዳማ ዞን የሚሊኒየሙን የልማት ግብ ለማሳካት በበጀት ዓመቱ ከ89 ሚልዮን ብር በሚበልጥ በጀት 25 የመጠጥ ውሃ ፐሮጀክት ግንባታ እንደሚካሄድ የዞኑ ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ መምሪያ ገለጸ፡፡ የመምሪያው ሃላፊ አቶ አብሩ ዳቃሞ ሰሞኑን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት ከፕሮጀክቶቹ መካከል 20ዎቹ ጥልቅ ጉድጓድ ቁፋሮ ቀሪዎቹ ማከፋፈያ፣ የማጠራቀሚያ ጋን፣ የውሃ ቦኖና ምንጭ ማጎልበት ናቸው፡፡ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶቹ የሚሰሩት በመንግስት፣ በዋሽ፣ በዩኒሴፍ ፕሮግራምና በህብረተሰብ ተሳተፎ መሆኑን ጠቁመው ወደ ስራ ለመግባት የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን አስታውቀዋል፡፡ ፕሮጀክቶቹ በተያዘው የበጀት ዓመት መጨረሻ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቀው አገልገሎት እንዲሰጡ ከዞን ምክር ቤት ጀምሮ በየደረጃው ለሚገኙ አመራር አካላትና ህብረተሰብ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት መስጠቱን ተናግረዋል፡፡ የፕሮጀክቶቹ ግንባታ ሲጠናቀቅ ከ380ሺህ የሚበልጡ የዞኑ ነዋሪዎች የመጠጥ ውሃ አገልግሎት ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ሃላፊው ጠቁመዋል፡፡ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶቹ በዞኑ 50 በመቶ ላይ የነበረውን አጠቃላይ የዞኑን የመጠጥ ውሃ ሽፋን ወደ 62 በመቶ እንደሚያሳድግ ገልጸዋል፡፡ በዞኑ ወረዳዎች በሚገኙ 32 ቀበሌዎች ለ2006 የበጀት ዓመት ከመንግስት በተመደበ 75 ሺህ ብር 312 ፕሮጀክቶች ጥናትና ዲዛይን ስራ 24 ተቋማት የጣራ ላይ ውሃ ማሰባሰብ፣ 2ሺህ ነባር ተቋማትን መልሶ የማደራጀት ስራዎች በመከናወን ላይ እንደሚገኝ አብራርተዋል፡፡ የቦርቻ፣ አለታ ወንዶና አለታ ጩኮ ወረዳ ነዋሪዎች በሰጡት አስተያየት መጠጥ ውሃ ፍለጋ ረጅም ርቀት በመጓዝ ያባክኑት የነበረውን ጊዜ ለልማት በማዋል ምርትና ምርታማነታቸውን ለመጨመር እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡ በ2004 በዞኑ አስራ ሁለት ወ

የሁለት ብሄሮችን ግጭት ማስተዳደር አቅቶኛል ያሉ ሰውዬ በየትኛው ቀመር የ80 ብሄሮች ቀንበር ይሸከማሉ ???

ጥቅምት 10 2005 ዓ.ም. ለንባብ የበቃው የሪፖርተር ጋዜጣ ልዩ ዕትም ለአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ የኋላ ታሪክ ሰፊ ሽፋን ሰጥቶ ብቅ ማለቱ ይታወሳል፡፡ የዘገባውን ተኣማኒነት ለማጎልበት ጋዜጣው የጠቅላይ ሚኒስትሩን የቀድሞ የሥራ ባልደረቦችንና ወዳጆች አግኝቶ ለማነጋገር ብዙ የደከመ ይመስላል፡፡  ሆኖም ግን ሪፖርተር ጋዜጣ የአቶ ኃይለማሪያምን ጠንካራ ጎን ለመዳሰስ ባደረገው ጥረት፤የጠቅላይ ሚኒስትሩን የመጠቅለል ብቃትን በጥርጣሬ ዓይን የሚያዩ  ወገኖች በግብዓትነት ሊጠቀሙበት የሚችሉትን መረጃዎችን ሳያቀብል አልቀረም፡፡  በእኔ እምነት ዘገባው አንባቢያን ዘንድ ሲደርስ በአዘጋጆቹ ዘንድ ፈጽሞ ያልተጠበቀን ትርጉም (unintended interpretation) የመስጠት አቅም አለው፡፡ ለምሳሌ አንዳንድ ወገኖች የአቶ ኃይለማሪያምን ከደቡብ ብሄር ብሄረሰቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደርነት ወደ ቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ቤተመንግስት ለመዛወራቸው በመንስኤነት የሚያስቀምጡት የአመራር ብቃታቸውን ማነስ ነው፡፡  ሪፖርተር ጋዜጣም ይህንኑ ግምት የሚያጠናክር መረጃን ነበር ይዞ ብቅ ያለው፡፡ የአቶ ኃይለማሪያም የእምነት ተምሳሌትና አማካሪ (Informal adviser) የነበሩ ቢሾፕ ሕዝቅኤል የሲዳማና የወላይታ ግጭት የአቶ ኃይለማሪያም አመራርን ክፉኛ ተፈታትኖት እንደነበረ በጋዜጣው ላይ በግልጽ ተናግረዋል፡፡  ጋዜጣው የቢሾፑን ምላሽ ያስቀመጠው እንደዚህ ነው፦ “አንድ ጊዜ በዚህ በሐዋሳ ጉዳይ አሁን አስቸጋሪውን ጉዳይ ለመወጣት እየሞከርኩ ነው ያለሁትና ጸልዩልኝ ብሎኝ ነበር፤የሚሉት ቢሾፑ አቶ ኃይለማሪያም እንዴት ከክልል ወደ ፌደራል መንግስት በአቶ መለስ ዜናዊ ጥሪ መሠረት እንደሄዱ ያብራራሉ…..” በዚህ ጉዳይ ላይ በጣ