Posts

በደቡብ የክልል የም/ቤትና የቀበሌ ምርጫዎችን ጨምሮ በአዲስአበባ የከተማ አስተዳደር፣የዞንና የወረዳ ም/ቤቶች ምርጫ በሚያዚያ ወር 2005 ለማካሄድ ቦርዱ አቅዶአል፡፡

ተቃዋሚዎች በዘንድሮ ምርጫ መዳከም አሳይተዋል ኢሳት ዜና:-ዘንድሮ ይካሄዳል ተብሎ በሚጠበቀው የአካባቢና የአዲስአበባ ከተማ ምርጫ ተቃዋሚዎች እስካሁን ምንም ዓይነትጥቅምት ፳፮ (ሀያ ስድስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ዝግጅት አለማድረጋቸውን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ገለጹ፡፡ ምርጫ ቦርድ በሕግ በተሰጠው ሥልጣን መሰረት ምርጫው የሚያካሄድበትን የጊዜ ሰሌዳ ባለፈው ሳምንት ይፋ ያደረገ ሲሆን በዚህ ጊዜ ሰሌዳ መሰረት ተወዳዳሪ ፓርቲዎች በምርጫው ዕጩዎቻቸውን ለማስመዝገብ የቀራቸው ጊዜ ሶስት ወራት ብቻ ነው፡፡ ይህም ሆኖ እስካሁን አንድም ፓርቲ በምርጫው እንደሚሳተፍ የገለጸበት ሁኔታ ካለመኖሩም በላይ ምርጫ ስለመኖሩም እየተነገረ አለመሆኑ ታውቋል፡፡ኢህአዴግ ሆን ብሎ ስለምርጫው ብዙም ሳይወራ በግርግር አሸናፊ ተብሎ እንዲያልፍ እንደሚፈልግ ምንጫችን አስታውሶ ተቃዋሚዎች ግን በአዲስአበባ እንኳን ጥቂትም ቢሆን ወንበር ለማግኘት ከወዲሁ መስራት አለመቻላቸው በጣም መዳከማቸውን እንደሚያሳይ ገልጾአል፡፡ትልቁን ተቃዋሚ ፓርቲ መድረክን ጨምሮ እንደ መኢአድ ያሉ ፓርቲዎች በምርጫው ለመሳተፍ እስካሁን አለመወሰናቸው ታውቋል፡፡ ይህ አጋጣሚ ደግሞ ለገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ አመቺ ሁኔታን ከመፍጠር ያለፈ ፋይዳ እንደሌለው የዜና ምንጫችን ጠቁሟል፡፡ አብዛኛዎቹ ፓርቲዎች ከምርጫው በፊት በአገሪቱ ካሉ የፖለቲካ ችግሮች ጋር በተያያዘ ለመወያየት ፍላጎት እንዳላቸው ከሳምንት በፊት በአዳማ ምርጫ ቦርድ በጠራው ስብሰባ ላይ ያሳወቁ ቢሆንም በምርጫ ቦርድ በኩል ያለው ዝምታ ግን ጊዜ መግደያ መሆኑን አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች እየተናገሩ ነው፡፡ ፓርቲዎቹ ለመወያየት ያቀረቡት ጥያቄ እንደተጠበቀ ሆኖ ለምርጫው እየተዘጋጁ ቢጠባበቁ የተሻለ ዕድል እንደሚኖራቸው ምንጫችን መክሮአል፡፡ይህ

የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ተጠናቀቀ

Image
የክልሎችን የ2004 እቅድ አፈጻጻም ማጠቃለያና የ2005 እቅድ ዝግጅትና ፈጻሚ ማዘጋጀት ስራዎችን በመፈተሽ ስብሰባውን የጀመረው ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ባለፈው አመት የገጠር ልማትን በተመለከተ በተፋሰስ፣ በመስኖና በሰብል ልማት ስራዎች አፈጻጻም የነበረው አንጻራዊ ልዩነት እንደተጠበቀ ሆኖ በሁሉም ክልሎች የተሻለ እንቅስቃሴና ውጤት መታየቱን አረጋግጧል፡፡ ይኸው አበረታች እንቅስቃሴ በ2005 የአርሶ አደሩን ምርታማነትና አጠቃላይ ሀገራዊ ምርትን ለማሳደግ የሚደረገው ርብርብ አዎንታዊ ድርሻ እንዳለው ገምግሟል፡፡ በማህበራዊ ልማት ዘርፍም በተለይም የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ሰፊ እንቅስቃሴ መደረጉንና በወላጅ፣ በመምህራንና በተማሪዎች የተደራጀ ጥረት አመርቂ ውጤት መታየቱን አረጋግጧል፡፡ የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራሙን በሰፊ የህዝብ ተሳትፎ በማስፋፋትና የእናቶችና ህጻናትን ሞት ለመቀነስና በአጠቃላይ ጤንነቱ የተጠበቀ ህብረተሰብ በመገንባት የጀመርነውን ፈጣን እድገትና የሀገሪቱን ህዳሴ ለማስቀጠል በተለይ የሴቶች አደረጃጀቶች ላይ ተመሰርቶ የተደረገው ጥረት ከፍተኛ ውጤት በማሳየቱ በሁሉም ክልሎች የተገኙትን ልምዶች በመቀመር አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥቶ መክሮበታል፡፡ ከመልካም አስተዳደር ጋር በተያያዘ በገጠሩ የተሻለ ሁኔታ መኖሩን የገመገመው ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው የተገኘውን ለውጥ መሰረት በማድረግና የተጀመረውን የህዝቡን ልማታዊ እንቅስቃሴ በማጠናከር በህዝቡ በራሱ ተሳትፎ አልፎ አልፎ የሚገጥሙ ችግሮችን ማስወገድ የሚችልበት ሁኔታ መፈጠሩን በመገምገም ከስምምነት ላይ ደርሷል፡፡ የከተማ ሰራዎችን በተመለከተ በዋነኝነት የከተማውን ነዋሪ የገቢ አቅም ለማሳደግ የተካሄደው የስራ እድል ፈጠራና የጥቃቅንና አነስተኛ ተ

ከሲዳማ ዞን በህገ ወጥ መንገድ የእሸት ቡና ወደ ሌሎች አካባቢ ሲያዘዋውሩ የተገኙ የሦስት የጭነት መኪናዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡

የጭነት መኪናዎቹ የተያዙት የዞኑ ፖሊሲ ከህብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማ በዘርፉ ከተቋቋመው ግብረ ኃይል በመተባበር ነው፡፡ የጭነት መኪናዎቹ ሦስት አይሱዚዎች ሲሆኑ ኮድ ሦስት ታርጋ ቁጥር 67218፣ 68896፣ እና 48 3ዐ7 አዲስ አበባ የሚሉ ናቸው፡፡ የሲዳማ ዞን ፖለሲ መምሪያ ህገ ወጥ የቡና ግብይትን ለመቆጣጠር በዞኑ ከተቋቋመው ግብረ ኃይል ጋር በመተባበር ባለፈው አርብ ከሌሊቱ 9 ሰዓት በተደረገው ክትትል ተሽከርካሪዎቹ በቁጥጥር ሲውሉ አሽከርካሪዎቹ አምልጠዋል፡፡ የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኢንስፔክተር ተስፋዬ ዴቢሶ አንደገፁት ቡና ጥራቱን ጠብቆ ለማዕከላዊ ገበያ ቀርቦ ለአገሪቱ ኢኮኖሚ እድገት የሚጫወቱት ሚና በተገቢው መልኩ እንዲወጣ ማድረግ ከተፈለገ ህገ ወጥ የንግድ እንቅስቃሴዎች ሊቆሙ ይገባል፡፡ የአገሪቱን ኢኮኖሚ የሚጐዱ የንግድ እንቅስቃሴዎችን የሚያደርጉ የንግዱ ማህበረሰብ ከድርጊታቸው ከወዲሁ ሊቆጠቡ እንደሚገባም አስገንዝበዋል፡፡ ድርጊቱን የማጋለጥ ሥራ በዞኑ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ኢንስፔክተር ተስፋዬ አልክተዋል፡፡ የሲዳማ ዞን ቡና አቅርራቢዎች ማህበር ምክትል ሊቀመንብር አቶ ቶንጐላ ቶርባ በሰጡት አስተያየት ቡና የአገሪቱ ኢኮኖሚ ዋልታ በሆኑ በዘርፉ የተሰማሩ በተቀመጠው ደንብና መምሪያ መሠረት መንቀሳቀስ ሲገባ ህገ ወጥ የንግድ እንቅስቃሴ የሚያደርገትን አጥብቀው እንደሚቃወሙ ተናግረዋል፡፡ ህገና ህጋዊነት ለማክበር መዘጀታቸውን በማረጋገጥ የዞኑ ግብይትና ህብረት ስራ መምሪያ ኃላፊ አቶ ቡርቃ ቡላሾ በበኩላቸው ማንኛውም የቡና ግብይት በተፈጠረላቸው የግብይት ማዕከላት ብቻ እንዲካሄድ የወጣውን ደንብ ወደ ጐን በመተው የተፈፀመ ድርጊት በቡና ጥራት ላይ አሉታዊ ተፅኖ የሚፈጥር ነው ብለዋል፡፡ በዞኑ እንዲሁ ዓይነት ድርጊት እንዳይፈጠር ለማድረግ በበጀት ዓመቱ

በሲዳማ ዞን ከ12 ሚልዮን ብር የሚበልጥ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወስደው ስራ ጀመሩ

Image
አዋሳ ጥቅምት 22/2005 በሲዳማ ዞን ባለፉት ሶስት ወራት ከ12 ሚልዮን ብር የሚበልጥ የኢንቨስትመንት ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች ፈቃድ ወስደው ወደ ስራ መሰማራታቸውን የዞኑ ንግድና ኢንዱስትሪ መምሪያ ገለጸ፡፡ በመምሪያው የኢንቨስትመንት ማስፋፊያ ዋና የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ብርሃኑ ወልደሚካኤል ትናንት ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በመጀመሪያ ሩብ ዓመት አራት ባለሃብቶች ፈቃድ በማውጣት ስራ ጀምረዋል፡፡ ባለሃብቶቹ ከተሰማሩባቸው የስራ መስኮች መካከል አገልግሎት መስጫ ተቋማት፣ ግብርናና ኢንዱስትሪዎች እንደሚገኙበት አስታውቀው ባለሃብቶቹ በጀመሩት የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ለ88 ቋሚና 894 ዜጎች ጊዜያዊ የስራ ዕድል ማግኘታቸውን ገልጸዋል። አንዳንድ ከተሞች ላይ ባለፈው ዓመት የተጀመረው የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ከአምስት ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች የስራ ዕድል መፍጠራቸውን አስታውቀዋል፡፡ መምሪያው ለ12 ባለሃብቶች የፈቃድ እድሳትና ተጨማሪ የማስፋፊያ ፈቃድ መሰጠቱን ጠቁመው ከዚህ ቀደም ቦታ ወስደው ወደ ስራ ያልገቡ ባለሃብቶችን በመከታተልና ድጋፍ በመስጠት በፍጥነት ወደ ስራ የሚገቡበትን ሂደት ለማመቻቸት ባደረገው ጥረት 32 ፕሮጀክቶች የአገልግሎት ተጠቃሚ ሆነዋል ብለዋል፡፡ በሲዳማ ዞን ባለፈው በጀት ዓመት ከ267 ሚልዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ 56 ባለሃብቶች በተለያዩ መስኮች የተሰማሩ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ብርሃኑ በተለይ በይርጋዓለም፣ በወንዶ ገነት፣ በሸበዲኖ፣ በለኩና በበንሳ ከተሞች የሚታየው የባለሃብቶች የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ አዲስ ፈቃድ ወስደው ወደ ስራ ከገቡት ባለሃብቶች መካከል አቶ ብርሃኑ አድማሱና ወይዘሪት ሶፋኒት አምዴ ልማታዊ መንግስት ለግል ኢንቨስትመንት እያደረገ ያለው ድጋፍ በርካታ

ሃዋሳን ጨምሮ በደቡብ ክልል በከተሞች ለነዋሪዎች ስኳር ስንዴና የምግብ ዘይት ተከፋፈለ

Image
አዋሳ ጥቅምት 22/2005 በደቡብ ክልል ከተሞች ገበያን ለማረጋጋት ባለፉት ሶስት ወራት 27ሺህ 475 ኩንታል ስኳርና ስንዴ እንዲሁም ከ613ሺህ ሊትር በላይ የምግብ ዘይት ለተጠቃሚው መከፋፈሉን የክልሉ ግብይትና ህብረት ስራ ቢሮ ገለፀ፡፡ የቢሮው የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች የስራ ሂደት ባለቤት አቶ መላኩ እንዳለ ትናንት ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት የፍጆታ ሸቀጦቹ የተከፋፈሉት ሀዋሳን ጨምሮ በክልሉ ከተሞች በሚገኙ 133 የሸማቾች ህብረት ስራ ማህበራት አማካኝነት ነው፡፡ ከተከፋፈለው መካከል 19ሺህ 345 ኩንታል ስኳር፣ 8ሺህ 130 ኩንታል ስንዴና ከ613ሺህ ሊትር በላይ የምግብ ዘይት ለአባላትና ለአካባቢው ህብረተሰብ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ ባለፉው የበጀት ዓመትም በ123 የሸማቾች ህብረት ስራ ማህበራት አማካኝነት ከ2 ነጥብ 5 ሚልዮን ሊትር በላይ የምግብ ዘይት፣ ከ533ሺህ ኩንታል በላይ ስኳር ፣ የምግብ እህልና የተለያዩ ሸቀጦች በተመሳሳይ ለተጠቃሚዎች መከፋፈሉን ገልጸዋል፡፡ http://www.ena.gov.et/Story.aspx?ID=3108