Posts

ምክር ቤቱ የሕዳሴ ጉዞን በሚያስቀጥሉ አቅጣጫዎችና ስልቶች ላይ ከስምምነት ደረሰ

Image
አዲስ አበባ፡- የኢህአዴግ ምክር ቤት ሕዝቡን በማሳተፍ የተጀመረውን ልማታዊና ዴሞክራሲያዊ የሕዳሴ ጉዞ ለማስጠቀል በሚያስችሉ አቅጣጫዎችና ስልቶች ላይ ከስምምነት ላይ ደረሰ። የኢህአዴግ ምክር ቤት ጽሕፈት ቤት ለዝግጅት ክፍላችን እንዳስታወቀው፤ የሕዳሴውን ጉዞ መላው የግንባሩ አባላትና የትግሉ ደጋፊዎች እንዲሁም የለውጡ ባለቤቶችና ተጠቃሚዎች የሆኑት መላው ኢትዮጵያውያንን በማሣተፍ ማስቀጠል እንደሚገባ ምክር ቤቱ ስምምነት ላይ ደርሷል። ትናንት የተጀመረው የኢህአዴግ ምክር ቤት ስብሰባ ለታላቁ የድርጅቱ ሊቀመንበር ለክቡር አቶ መለስ ዜናዊ የሕሊና ፀሎት በማድረግ ተከፍቷል። ከአራቱ ብሔራዊ ድርጅቶች በእኩል ድምፅ የሚወከሉት የምክር ቤቱ አባላት ምልዓተ ጉባኤ መሟላት መሠረት በማድረግ ከሕሊና ፀሎቱ በኋላ ለምክር ቤቱ በመወያያነት በቀረቡት አጀንዳዎች ዙሪያ ተወያይቶ በማፅደቅ ሥራውን ጀምሯል። በዚሁ መሠረት በሁለቱ ቀናት ምክር ቤቱ ለመወያየት ከያዛቸው አጀንዳዎች መካከል በቅድሚያ፡-የሚመክረው የልማታዊ ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብ ተግባራዊ ልዕልናን በማረጋገጥ የመለስ/ኢህአዴግን ራዕይ ለማሳካት እንረባረብ በሚል ርዕስ የተዘጋጀና በታላቁ መሪና በድርጅቱ አመራር የተገኙትን ስኬቶች ማስቀጠል በሚቻልባቸውና ቀጣይ ፈተናዎችን ለመቋቋም በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ ነው። ከዚህ በማስቀጠልም ታላቁ መሪ በሕይወት በነበሩበት ጊዜ ተዘጋጅቶ በሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ውይይት ተደርጎበት የነበረው የአመራር ግንባታና የሕዳሴው ጉዞ በሚል ርዕስ ኪራይ ሰብሳቢነትን ከምንጩ ለማድረቅና የሕዝቡን ዘላቂ ጥቅምና ተጠቃሚነት በሕዝቡ የተደራጀና ቀጣይነት ያለው ንቅናቄና ተሣትፎ ማረጋገጥ ይቻል ዘንድ እና ከዚሁ ሂደት ጠንካራ የድርጅትና መንግሥት አመራር መፍጠር በሚቻልባቸው የአሠራር የአደረጃ

የኢህአዴግ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳች ላይ እየመከረ ነው

አዲስአበባ፣መስከረም4 2005 (ኤፍቢሲ) ምክር ቤቱ  በመጀመሪያ  ቀኑ  የጉባኤው ውሎ ከጠቅላይ  ሚኒስትር  መለስ ዜናዊ ህልፈት በኋላ በአገራችንና  በአከባቢው እንዲሁም በሌሎች የዓለም ክፍሎች የተፈጠረውን ሁኔታ  ገምግሟል ። ከዚህ በመነሳትም በአገራችን መካሄድና ይበልጥ መጠናከር ያለበትን የልማታዊ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት  ግንባታን አጠናክሮ ማስቀጠል በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ዛሬ መክሯል ። መላውን የድርጅቱን አባላትና የትግሉን ደጋፊዎች እንዲሁም የለውጡ ባለቤቶች እና ተጠቃሚዎች የሆኑትን መላውን የኢትዮጵያ ህዝቦችን በማሳተፍ የተጀመረውን ልማታዊና ዲሞክራሲያዊ የህዳሴ ጉዞ ለማስቀጠል በሚያስችሉ አቅጣጫዎችና ስልቶች  ዙሪያም በመወያየት ከስምምነት ደርሷል ። የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር /ኢህአዴግ/ ምክር ቤት እስከ ነገ  በሚቆየው ስብሰባ የድርጅቱን ሊቀመንበር ይሰይማል። በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ አፈፃፀም ዙሪያ ያካሄደውን አጭር ግምገማና የ2005 ዓ.ም የትኩረት አቅጣጫዎች የሚመለከት ሰነድ በመመርመር ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ታውቋል። ምክር ቤቱ በአቶ መለስ ዜናዊ አመራርና በድርጅቱ የተጀመረውን የኢትዮጵያ ህዳሴ አጠናክሮ ለማስቀጠል የድርጅቱን የአመራር ግንባታ በተመለከተ የተዘጋጀውን ሰነድ በመመርመር መሰረታዊ አቅጣጫዎችን እንደሚያመላክትም የምክር ቤቱ ፅህፈት ቤት  ለፋና ብሮድካሲትንግ ኮርፖሬት በላከው መግለጫ ላይ ጠቅሷል ። የኢሕአዴግ ምክር ቤት ከአራቱ አባል ድርጅቶች በእኩል የተሰየሙ 180 አባላት ያሉት ሲሆን በሁለት ጉባዔዎች መካከል የግንባሩ ከፍተኛ የሥልጣን አካል ሆኖ ያገለግላል ።

The Political Economy of the Sidama Regional Question-Overview

Image
By Hawassa Teessonke September 13, 2012 Today, the Sidama people are at a crossroads. Structural economic weaknesses and lack of economic transformation amid massive over population has left the majority of the population in abject poverty. Unemployment, particularly among the youth, and rural underemployment remain rampant. The continued economic marginalization amid relative improvements in political space since 1991 has been worsened by lack of capacity and good governance, corruption, and above all disempowering administrative arrangement that denied political voice to the majority of the population. The country has adopted bicameral administrative system since 1993. While the majority of the country is organized in a federal system in line with ethno-linguistic affiliations and delineations; over 45-50 ethnic groups in the South are forcefully lumped together under the Southern Ethiopia Peoples’ Region. Accordingly to the July 1,  2012 population estimate by t

የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር /ኢሕአዴግ/ የድርጅቱን ሊቀመንበር እሁድና ቅዳሜ በሚያካሂደው ስብሰባ ይሰይማል

Image
New አዲስ አበባ መስከረም 3/2005 የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር /ኢሕአዴግ/ ምክር ቤት የፊታችን እሁድና ቅዳሜ አዲስ አበባ ውስጥ በማካሄድ የግንባሩ ሊቀመንበርና ምክትል ሊቀመንበር ይሰይማል፡፡ የግንባሩ ጽህፈት ቤት ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንዳስታወቀው የምክር ቤቱ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ መስከረም 5 እና 6 ቀን 2005 ዓ.ም ስብሰባውን በማድረግ በቅርቡ በድንገት የተለዩትን ታላቁ መሪውን የሚተካ የግንባሩ ሊቀመንበር እንዲሁም ምክትል ሊቀመንበር የሚሰይም ሲሆን ሌሎች ከዚሁ ጋር ተያያዥነት ባላቸው ጉዳዮች ላይ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል። በዚሁ ወቅት በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ አፈፃፀም ዙሪያ ያካሄደውን አጭር ግምገማና የ2005 ዓ.ም የትኩረት አቅጣጫዎች የሚመለከት ሰነድ በመመርመር ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ታውቋል። ለሁለት ቀናት በሚካሄደው የምክር ቤቱ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ የ2005 ዓ.ም በድርጅትና በፖለቲካ ሥራዎች ዙሪያ መክሮ መሰረታዊ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል። ምክር ቤቱ በታላቁ መሪ በሳል አመራርና በድርጅቱ የተጀመረውን የኢትዮጵያ ህዳሴ አጠናክሮ ለማስቀጠል የድርጅቱን የአመራር ግንባታ በተመለከተ የተዘጋጀውን ሰነድ በመመርመር መሰረታዊ አቅጣጫዎችን ያመላክታል። የኢሕአዴግ ምክር ቤት ከአራቱ አባል ድርጅቶች በእኩል የተሰየሙ 180 አባላት ያሉት ሲሆን በሁለት ጉባዔዎች መካከል የግንባሩ ከፍተኛ የሥልጣን አካል ሆኖ እንደሚያገለግል የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዘገባ አመልክቷል፡፡ http://www.ena.gov.et/story.aspx?ID=2439

Ethiopian coffee farmers to tour schools, speak to the public

Image
ROSEMARY BEACH — Multinational coffee companies have built an industry worth more than $80 billion a year, and coffee has become the most valuable trading commodity in the world after oil. But until recent years, little of that money made its way to the root of the industry: the small farmer struggling to survive in places such as Ethiopia. That’s why Dan Bailey, owner of Panama City Beach-based Amavida Coffee and Trading Co., thinks it is important to tell the story of the cooperatives that have helped funnel more money toward the farmers and raise their standard of living. “It’s important to really understand how connected we are to the rest of the world through our purchases,” Bailey said, “for the public to understand how they buy and what they buy can help contribute” to efforts like eliminating poverty, creating sustainable businesses, and supporting education, health care and gender equality in developing nations. To that end, Amavida is hosting representatives of