Posts

ተቋሙ በተያዘው የበጀት ዓመት ከ1ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ ሊያበድር ነው

አዋሳ ነሐሴ 05/2004 በደቡብ ክልል በተያዘው የበጀት ዓመት ቁጠባን መሰረት ያደረገ ከ1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ የብድር ገንዘብ ለተጠቃሚዎች ማመቻቸቱን የኦሞ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም አሰታወቀ፡፡ በክልሉ በሚገኙ የገጠርና የከተማ ቀበሌዎች የተጀመረው የቁጠባ ኤክስቴንሽ አገልግሎት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተመልክቷል፡፡ የተቋሙ የህዝብ ግንኙነት ክፍል ሀላፊ አቶ ሰሎሞን ገለቱ ትናንት ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንዳስታወቁት ብድሩ የተመቻቸው ሀዋሳን ጨምሮ በክልሉ ሁሉም ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ተደራጅተውና በግል ስራ ፈጥረው ለሚንቀሳቀሱ ከ200 ሺ በላይ ተጠቃሚዎች ነው፡፡ ለስራቸው ማጠናከሪያና ማንቀሳቀሻ የሚሰራጨው ይሄው የብድር ገንዘብ ለእያንዳንዳቸው ከ5 ሺ እስከ 100 ሺ ብር የሚሰጥ መሆኑን አመልከተው ሰርተውበት ከአንድ እስከ ሁለት ዓመት ባለው ጊዜ ተመላሽ እንዲያደርጉ የክትትልና የሙያ ድጋፍ እንደሚሰጣቸው አስረድተዋል፡፡ ባለፉት ዓመታት በተመሳሰይ ሲሰጥ የቆየው የብድር ገንዘብ በአብዛኛው ተመላሽ መደረጉን ያመለከቱት ኃላፊው ህብረተሰቡ የወሰደውን የብድር ገንዘብ በአግባቡ በመጠቀም በወቅቱ የመመለሱ ባህሉ እየዳበረ መምጣቱን ገልጸዋል፡፡ እንዲሁም ከ896 ሺ በላይ አዲስና ነባር ደንበኞች ላይ ከ1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በላይ በቁጠባ ለማሰባሰብ መታቀዱንም ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም ባለፈው የበጀት ዓመት በክልሉ በሚገኙ ቀበሌዎች ባለሙያዎች በመመደብ የተጀመረው የገንዘብ ቁጠባ ኤክስቴንሽን አገልግሎት በዚህ ዓመትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አቶ ሰሎሞን አመልክተዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት አገልግሎቱ በክልሉ የተለያዩ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች በሚገኙ ከ3 ሺ በላይ የገጠርና የከተማ ቀበሌዎች መጀመሩን አመልከተው እስካሁንም ከ120 ሺ በላይ የቁጠባ ሳጥኖች ለተጠ

“በክር ሥራ ጀምራ በናይሮቢ ሱቅ የከፈተች የሃዋሳ ወጣት

Image
ፎቶ ኣዲስ ኣድማስ ፍላጐት እውቀትና ሙያ፣ ጉልበትና በራስ መተማመን እንጂ፣ ቤሳ ቤስቲን አልነበራትም፡፡ አንድ የቤትና የቢሮ ቁሳቁስ ማምረቻ ድርጅት ሄዳ ጣውላ በዱቤ እንዲሸጡላት ጠየቀች፡፡ የድርጅቱ ባለቤት ወጣቷ ሴት በድፍረትና በልበ ሙሉነት ባቀረበችላቸው ጥያቄ ቢገረሙም፣ “ከየት አምጥተሽ ልትከፍይኝ ነው? አይሆንም” አላሉም፡፡ “እሺ ውሰጂ” አሏት፡፡ ድርጅቱ የሽመና መሳሪያ አምርቶ አያውቅም፡፡ ስለዚህ ራሷ የመሸመኛውን፣ የማድሪያውን፣ የምርት መጠቅለያውን ዲዛይን ሠርታና እንጨት ገጣጥማ እያሳየች አሠራች፡፡ ክር መሸጫ ሄዳ በዱቤ፣ የ80 ብር ክር ወስዳ፣ በሽመና መሳሪያው ክሩን ወደ ጨርቅነት ለወጠችው፡፡ ከዚያም ጨርቁን ቆራርጣ መንገድ ዳር አሰፋች፡፡ በገና 1995 በዓል ዕለት ሰባት የሰፈር ሕፃናት ሰብስባ ያሰፋቻቸውን ልብሶች አልብሳ ለቀቀቻቸው - ሳትታዘዝ፡፡ የአራቱ ልብሶች ዋጋ ወዲያው ሲከፈላት ሦስቱ በዱቤ ተሸጡ፡፡ መቶ ብር በማይሞላ የክር ዱቤ ሥራ ጀምራ ዛሬ ከግማሽ ሚሊዮን (500,000) ብር በላይ፣ እንዲሁም የተለያዩ ማምረቻ መሳሪያዎች ስለተገዙ በደንብ ሂሳብ ከተሠራ ከተጠቀሰው በላይ (ኧረ በግምት ሚሊዮን ሳይደርስ ይቀራል ብላችሁ ነው?) ካፒታል እንዳላት ተናግራለች - ወጣት ዙፋን ኢብራሂም፡፡ ይህ ብቻም አይደለም፡፡ ምርቶቿን በምሥራቅ አፍሪካ እያስተዋወቀች መሆኑን ተናግራለች፡፡ በናይሮቢ - ኬንያ አስሊ 10th street እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ምርት ማሳያና መሸጫ ሱቅ መክፈቷን ገልፃለች፡፡ ዙፋን፣ በታንዛኒያም ተመሳሳይ ሱቅ ለመክፈት ሐሳብ እንዳላት ገልፃለች፡፡ ዙፋን፣ ወላጆቼ እኔን ከሙዚቃ ለመለየት ኢትዮ ስዊድሽ ሕፃናትና ወጣቶች ማረሚያና ማቋቋሚያ ፕሮጀክት ቢያስገቡኝም፣ ዛሬ፣ ኢትዮ ስዊድሽ መተዳደሪያ ሆኖኛል ትላለች፡፡ ም

ኢትዮጵያ ከሶስት አመት በኋላ በምግብ ዋስትና ራሷን እንደምትችል ተጠቆመ

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 4፣ 2004 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ ከሶስት አመት በኋላ በምግብ ዋስትና ራሷን እንደምትችል የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ። በእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ መሰረት የዛሬ ሶስት አመት፤ ከ400 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የግብርና ምርት በዓመት የማምረት አቅም ይፈጠራል ተብሎ ይጠበቃል። ሚኒስትሩ አቶ ተፈራ ደርበው ይህን እቅድ ለማሳካት የሚያስችል አሰራር እየተዘረጋ መሆኑን ለፋና ብሮድካስቲነግ ኮርፖሬት ተናግረዋል። እቅዱ በይፋ በተጀመረበት በ2003 ዓመተ ምህረት ከዋና ዋና ሰብሎች የተገኘው 203 ሚሊዮን ኩንታል የግብርና ምርት በልማት እቅዱ ከተቀመጠው የዘጠኝ በመቶ እድገት አሳይቷል። በተመሳሳይ በ2004 ዓመተ ምህረት 218 ሚለዮን ኩንታል የምርት መጠን ለማግኘት ታስቦ እቅዱን ሙሉ ለሙሉ ማሳካት መቻሉን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።     ለእቅዶቹ መሳካት ደግሞ በዋነኝነት አርሶ አደሩን በልማት ሰራዊት በማደራጀት ንቅናቄ መፈጠሩ በምክንያትነት ተቀምጧል። በቀጣይነት ይህን የተደራጀውን አርሶ አደር አቅም መገንባት ከተቻለም እቅዱን ለማሳካት አያዳግትም ባይ ናቸው። በኢትዮጵያ አምስት ሚሊዮን ሄክታር የሚደርሰው መሬት በመስኖ ሊለማ ይችላል። ከዚህ ውስጥ 1 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሄክታር ያህሉ በአነስተኛ መስኖ የሚለማ ሲሆን ፥ ቀሪው ደግሞ በመካከለኛና በከፍተኛ መስኖ ሊለማ የሚችል ነው። አሁን እየታየ የሚገኘው የምግብ እህል የዋጋ ንረትም እንደሚረጋጋ ጠቁመው ፥ በመንግስት በኩል ይህን የዋጋ ማሻቀብ ለመቀልበስ ዋና ዋና የግብርና ምርቶች ወደ ውጭ እንዳይላኩ ከመከልከል ጨምሮ ብዙ የፖለሲ እርምጃዎች እንደተወሰዱ መናገራቸውን ታደሰ ብዙአለም ዘግቧል።  http://www.fanabc.com/Story.aspx?ID=25312&K=

የያዬ ሃርቤጎና ሃይድሮ ኤለክትሪክ ማምንጫ ከየት ደረስ?

Image
በሲዳማ ልማት ኮፖሬሽን ባኃላ ላይ የሲዳማ ልማት ኣክሽን ተብሎ በተሰየመው የልማትድርጅት ለምቶ ኣገልግሎት ይሰጥ የነበረው እና ኣሁን ያለበት ደረጃ  የማይታወቀው  የያዬ ሃርቤጎና ሃይድሮ ኤለክትሪክ ማምንጭን በተመለከተ ከታች ካለው ሊንክ ላይ ተጭናችሁ ኣንብቡ። የሃርቤጎና ሃይድሮ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ የሃርቤጎና ያዬ ኃይድሮ ኣኤክትሪክ ማመንጫ እንደ ፈረንጆቹ ዘመን ኣቆጣጠር በ2006 የቢቢስ World Challenge ተፎካካር እንደነበር ያውቁ ነበር? የኃይልማመንጫውን በተመለከተ በBBC የተዘጋጀውን ድክሜንታሪ በዚህ ሊንክ ተጭነው ይመልከቱ   Some eight hours' drive from the Ethiopian Capital Addis Ababa is the small community of Yayee. The surrounding countryside is a far cry from Ethiopia's stereotypical image: lush green pastures interwoven with rivers and streams. But this idyllic appearance is deceptive. Until the 1990s, political and economic marginalisation had rendered Yayee one of the poorest communities in Ethiopia. At the overthrow of the Marxist regime in 1991, just 23 percent of Yayee's children were attending school and the community had no medical facilities whatsoever. It was then that the people of Yayee decided to help themselves to a better s

ጊዳቦ ፍልውሃ ገና ያልተነካ እምቅ የተፈጥሮ ሀብት በአግባቡ ለመጠቀም

Image
ቅዱስ ኃይሉ ይርጋለሞች፣ ዳሌዎች እንዲሁም እነዚህን አካባቢዎችና የተለያዩ አገልግሎታቸውን ያዩ ሁሉ ሳይቋደሱት አያልፉም። የጊዳቦ ፍልውሃን በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች ክልላዊ መንግሥት ሲዳማ ዞን ዳሌ ወረዳ ይርጋለም ከተማ የሚገኘው ይህ የፍልውሃ ቀደም ሲል በዋቢ ሸበሌ ሆቴሎች አስተዳደር ሥር ይተዳደር ነበር። አሁን ደግሞ የሲዳማ ልማት ማኅበር ተቋም ነው። በተለያዩ አጋጣሚዎች ወደ እዚህ አካባቢ በሄድኩ ቁጥር እኔም ይህንን ሀብት ሳልቋደስ አልመለስም። በቅርቡም ወደዚሁ ፍልውሃ አገልግሎት ዘልቄ ያለፈውን እያስታወስኩ የአሁኑን አገልግሎቱን ቃኘሁ። ወደፊትም ሊኖረው የሚችለውን አቅምም ተንብያለሁ።  የፍልውሃ አገልግሎቱን ተጠቃሚ የሚያደርገውን ትኬት የሚቆርጡበት ቢሮ ቀድሞ ከነበረበት ወደ መግቢያው አካባቢ መጥቷል። ራሱን የቻለ ቤትም የፍልውሃ አገልግሎት መስጫ ቤቶቹ ከራስጌያቸው ያደረጉት ኮረብታውን ጥግ ይዞ ተሠርቶለታል።  የፍልውሃ አገልግሎቱ ሁሌም በወረፋ የተጨናነቀ መሆኑን ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት ቀን ምሳ ሰዓት ላይ ነው ወደ ሥፍራው ያቀናሁት። በእኔ ቤት ብልጥ ሆኜ ቶሎ አገልግሎቱን አግኝቼ ልመለስ።  የትኬት መቁረጡ ተራ እስኪደርሰኝ ድረስ ዙሪያ ገባውን ተመለከትኩት። ትኬቱ የሚቆረጥበት ሥፍራ ፍልውሃው የሚገኝበትን አካባቢ በሙሉ ለመቃኘት ያስችላል።  ቁልቁል ስመለከት የጊዳቦ ወንዝ ግራ ቀኙን በልምላሜ ታጅቦ በርበሬ መስሎ መፍሰሱን ተያይዞታል። ወቅቱ ክረምት ነውና የውሃው መጠን በጣም ጨምሯል፤ የሚጣደፍ አይመስልም። ድምፁ አይሰማም ከወንዙ ባሻገር የአርሶ አደሮች መንደር፣ እንሰት፣ ዛፎች እና የተለያዩ ተክሎች ይታያሉ። ከነዚህ ተክሎች ውስጥ ቡናና የፍራፍሬ ዛፎች ሊገኙበት እንደሚችሉ ጠጋ ብዬ ያየኋቸው የከተማና የገጠር መኖሪያ ጊቢዎች