Posts

ሃዋሳ የከተማ አውቶብስ ትራንስፖርት አገልግሎት ልትጀምር ነው

Image
ሀዋሳ ፣ ሀምሌ 20፣ 2004 (ኤፍ ቢ ሲ) ሃዋሳ የከተማ አውቶብስ ትራንስፖርት አገልግሎት ልትጀምር ነው። በቅርቡም አራት አውቶብሶች ገብተው ስራ እንደሚጀምሩ ነው የከተማዋ አስተዳደር  ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት  የገለፀው ። አውቶብሶቹ ከከተማዋ ውጭ ለሚገኙ አዋሳኝ ከተሞችም የትራንስፖርት አገልግሎት ይሰጣሉ ። የከተማዋ አስተዳደር እንደሚለው ለነዋሪዎች የትራንስፖርት አማራጭ ከመስጠትም ባለፈ በከተማዋ ቀስ በቀስ ደረጃቸውን በጠበቁ የትራንስፖርት አገልግሎት ለማቅረብ ያስችላል ። አውቶብሶቹን ስራ ለማስጀመር 24 የማቆሚያ ፌርማታዎች ተለይተዋል። በአሁኑ ወቅት በከተማዋ የትራንስፖርት አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ ከ3 ሺህ በላይ የሚበልጡ ተሽከርካሪዎች ሲኖሩ ፥ ከእነዚህ ውስጥ አብዛኛዎቹ ባጃጆች ናቸው። የአስተዳደሩ የትራንስፖርት ፅህፈት ቤት እንደሚለው የአውቶብሶቹ ወደ ከተማዋ መግባት ነዋሪው አማራጭ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲያገኝ ያስችላል ፤ ዘገባው የታደሰ ብዙዓለም ነው።

የአስራ ሁለተኛ ክፍል መሰናዶ ተማሪዎች የፈተና ውጤት ይፋ ሆነ ፤ ለሲዳማ ተማሪዎች መልካም እድል እንመኛለን

አዲስ አበባ፣ ሀምሌ 20፣ 2004 (ኤፍ ቢ ሲ) የአስራ ሁለተኛ ክፍል መሰናዶ ተማሪዎች የፈተና ውጤት ዛሬ ረፋድ ላይ በሀገር አቀፍ ፈተናዎች ድርጅት ድረ ገጽ ይፋ ተደረገ። ፈተናውን የወሰዱ ተማሪዎች ውጤታቸውን በሀገር አቀፍ ፈተናዎች ድርጅት ድረ ገጽ  WWW. nae.gov.et  መመልከት ይችላሉ። በ2004 ዓ.ም ወደ ዪኒቨርሲቲ መግቢያ ሀገር አቀፍ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ቁጥር 156, 997 ነው። የሀገር አቀፍ ፈተናዎች ድርጅት ዋና ዳይሬክተር አቶ አራዓያ ገብረእግዚአብሔር ዛሬ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንዳስታወቁት የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ነጥብ በአስራ አምስት ቀናት ውስጥ ይፋ ይደረጋል።

ከሃዋሳ -ጐፋ ፣ ከሃዋሳ – አርባ ምንጭ፣ ሃዋሳ -ተርጫ አዳዲስ የትራንስፖርት መስመሮች ተከፈቱ

Image
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 21/2004 (ዋኢማ) -  በደቡብ ክልል ባለፈው የበጀት ዓመት የተከፈቱት 11 አዳዲስ የትራንስፖርት መስመሮች የአካባቢውን ሕዝብ የተሻለ አገልግሎት እንዲያገኝ አስችለውታል። ነዋሪዎቹም ይህንን የሚመሰክሩት አዳዲስ የትራንስፖርት መስመሮች እንዲከፈቱና የተከፈቱትንም እንዲጠናከሩ በማሰባሰብ ጭምር ነው። መነሻቸውን ሃዋሳ መናኸሪያ ካደረጉና ወደተለያዩ አካባቢዎች ከሚጓዙ ተሳፋሪዎች መካከል ወደ አርባ ምንጭ ከተማ ለማቅናት በዝግጅት ላይ ያገኘናቸው ወይዘሮ መሰለች መስቀል ከዚህ በፊት ከነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት አቅርቦት ጋር ሲያነፃፅሩት በአሁኑ ወቅት ምቹ ሁኔታ መኖሩን ይጠቁማሉ። «ከዚህ በፊት ከሃዋሳ ወደ አርባ ምንጭ በተቆራረጡ መስመሮች ነበር የምንጓዘው። በዚህ ምክንያት ላልተፈለገ ወጪ፣ ለጊዜ ብክነትና ለእንግልት እንዳረግ ነበር» የሚሉት ወይዘሮዋ፤ በአሁኑ ወቅት ግን አዲስ መስመር ተከፍቶ አገር አቋራጭ አውቶቡስ በመመደቡ ችግሮቹ መቃለላቸውን ተናግረዋል። እንደ ወይዘሮ መሰለች ገለፃ፤ ከዚህ በፊት በቅጥቅጥ ተሽከርካሪ ወይም በተለያዩ የተሽከርካሪ ዓይነቶች ከሃዋሳ – አርባ ምንጭ ከ85 ብር በላይ ክፍያ ይጠየቅ፣ ጉዞውም ከስምንት ሰዓት በላይ ይወስድ ነበር። በአሁኑ ወቅት በአገር አቋራጭ አውቶቡሶቹ ለመጓዝ የሚጠየቀው ክፍያ 81 ብር መሆኑንና ጉዞውንም ከስድስት ሰዓት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ ማጠናቀቅ ይቻላል። ከዚህ በፊት ተገልጋዩ ከተሣፈረ በኋላ ከታሪፍ ዋጋ በላይ ጭማሪ የሚደረግበት ሁኔታ እንደነበር አመልክተው፤ የአዳዲስ መስመሮች መከፈት እነዚህንና መሰል ችግሮች ማስወገዱን ይገልፃሉ። ተገልጋዩ ጥሩ መስተንግዶ እንደሚያገኝም ይናገራሉ። «አዳዲስ የትራንስፖርት መስመሮች ከተከፈቱ በኋላ የተመደቡት አገር አቋራጭ ተሽከርካሪዎች የተሳፋሪው

የደቡብ ክልል ምክር ቤት ለ2005 በጀት ዓመት ከ14 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት አጸደቀ

Image
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 21/2004 (ዋኢማ) -  የደቡብ ክልል ምክር ቤት በ2005 በጀት ዓመት ለሚከናወኑ የመደበኛና ካፒታል ፕሮጀክቶች ማስፈጸሚያ ከ14 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት አጸደቀ። የጸደቀው በጀት ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ4 ቢሊዮን ብር ብልጫ ያለው ነው። በክልሉ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይለብርሃን ዜና እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ በክልሉ ለሚከናወኑ የተለያዩ የመደበኛና ካፒታል ፕሮጀክቶች ማስፈጸሚያ የተመደበው በጀት ብር 14 ቢሊዮን 14 ሚሊዮን 594 ሺህ 988 ብር ነው። የበጀቱ ምንጭም ከፌዴራል መንግስት ድጎማና ከከልሉ የሚሰበሰብ ገቢ ነው፡፡ በጀቱ ለክልል ማዕከል መስሪያ ቤቶች መደበኛና ካፒታል ወጪ፣ ለዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ጥቅል በጀት፣ ለክልላዊ ፕግራሞች፣ ለሚሊኒየሙ ግብ ማስፈጸሚያና ለክልሉ መጠባበቂያ በተዘጋጀው የበጀት ማከፋፈያ ቀመር መሰረት የተደለደለ መሆኑን ገልጸዋል። የክልሉ መንግስት ለ2005 የበጀት ዓመት ያጸደቀው በጀት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት የ4 ቢሊዮን ብር ብልጫ ያለው ሲሆን ይህም በክልሉ የሚከናወኑ የልማት፣ የመልካም አስተዳደርና ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ስራዎችን አጠናክሮ ለማሰቀጠል የሚያሰችል መሆኑ ተገልጿል። በተጨማሪም ጉባኤው በዛሬ ውሎው የክልሉ መንግስት የ2005 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ተወያይቶ ያጸደቀ ሲሆን በክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤትና በኦዲት ቢሮ የዕቅድ ክንውን ላይ በመወያየት ዛሬ ማምሻውን ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።

An Overview of the Sidama Resistance Movements

Image
...Various armed groups began to wage armed struggle to uproot the remnants of the Abyssinian regime from the Sidama land. Notable among these fighters and Sidama freedom leaders were: Yetera Bole, Wena Hankarso, Hushsula Xaadisso, Mangistu Hamesso and Lanqamo Naare and Fiisa Fichcho... ... The Sidama people had never accepted the Abyssinian conquest peacefully. They made various attempts to repulse the invading army. The first group of intruders led by Menelik's general Beshah Aboye were annihilated by the Sidama army and civilians led by the ingenious King of Sidama called Baalichcha Worawo. The army of Beshah was totally defeated and left in disarray until the second wave of attack was launched on by Leulseged, another general of Minelik, with superior military force on the Eastern front of Sidama. It was Leulseged's army which was able to establish full Abyssinian domination in the Sidama land and assassinate Baalichcha Worawo, the last king of Sidama. The patte