Posts

Showing posts from November, 2013

የሲዳማ ዞን ኣስተዳደር ለወጣቶች የስራ እድል ፈጥራለሁ ኣለ

በሲዳማ ዞን ዘንድሮ ከ72 ሺህ የሚበልጡ ወጣቶች የስራ እድል ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዷል   ሐዋሳ ህዳር 20/2006 በሲዳማ ዞን በተያዘው ዓመት ከ72 ሺህ የሚበልጡ ስራ አጥ ወጣቶች በገጠር ስራ እድል ፈጠራ እና ልማት ፕሮግራም ተጠቃሚ እንደሚሆኑ የዞኑ ዋና አስተዳደሪ ገለጹ፡፡ የዞኑ የገጠር ስራ እድል ፈጠራና ልማት ጽህፈት ቤት ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሂደዋል፡፡ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አክሊሉ አዱላ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች፣ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት፣ ከግል ኮሌጆችና አስርኛ ክፍል ላጠናቀቁ ዜጎች ሰፊ የስራ እድል ተዘጋጅቷል፡፡ ሃገራዊም ሆነ ክልላዊ የምጣኔ ሃብታችን እድገት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የገጠር ስራ እድል ፈጠራና ልማት እንቅስቃሴ ለማሳካት የሚያስችሉ ጠንካራ ስልቶች ተግባራዊ ማድረግ ወሳኝ በመሆኑ በየደረጃው የሚገኙ የባለድርሻ አካላት ጠንክረው መስራት እንዳለባቸው ጠቁመዋል፡፡ ሀገሪቱን መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሃገሮች ተርታ ለማሰለፍ በመንግስት በኩል ልዩ ትኩረት ከተሰጣቸው ልማታዊ እንቅስቃሴዎች አንዱ ለዜጎች ሰፊ የስራ እድል በመፍጠር ዘርፉ ውጤታማ እንዲሆኑ ማስቻል ቁልፍ ጉዳይ በመሆኑ ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰራ ይገባዋል ብለዋል፡፡ ለዘርፉ ወቅታዊ ድጋፍና ክትትል ማድረግ በግብርና የሚመራው ክፍለ ኢኮኖሚ ወደ ኢንዱስትሪ ለማሸጋገርና ልማታዊ ባለሃብቶችን ለመፍጠር ከሚያበረክተው አስተዋጽኦ ባሻገር ስራ አጥነትንና ድህነትን ለመቅረፍና ስራ ፈጣሪ ዜጎችን ለማፍራት ያለው ጠቀሜታ ከፍተኛ በመሆኑ ሁሉም መረባረብ እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡ በዘርፉ የሚታዩ ችግሮችን ከመሰረቱ ለመቅረፍ የአመራርንና የባለሙያውን አመለካከት ከመቀየር አኳያ ከ100 ሺህ ለመበልጡ የዞን፣ የወረዳና ለቀበሌ አመራሮች የአቅም ግንባታ ስልጠና

Opticians set sights on helping People near Hawassa

Image
An optician and lab technician from Ellesmere Port travel to Ethiopia this week to give vital aid to people who don’t have access to eyecare. Optometrist Alex Whitter and lab technician Mike Horsefield, who both work in the Ellesmere Port Specsavers store, will be travelling to villages near Hawassa to give much-needed eye tests and glasses to the locals. They aim to test at least 1,200 people. Working with Vision Aid Overseas (VAO), they will also be helping to train optometry students at Hawassa University. Another item on their agenda is to teach individuals to make their own glasses, to help the locals become self-sufficient and improve the level of eyecare in the area. This will be Alex’s sixth trip with the charity, and he is the team leader of the group, which consists of five optometrists from all over the UK. Mike will be glazing and dispensing the glasses. The visit will be Matt’s first VAO trip to Ethiopia and he is being sponsored by Specsavers. Store direct

''ከ1997 ምርጫ ቀደም ብሎ ተስፋ ይታይበት የነበረው የኢትዮጵያ ፖለቲካ፣ ምህዳር በምርጫው ምክንያት በተፈጠረው ቀውስ ከምርጫው በፊት ወደነበረበት አስከፊ ሁኔታ ተመልሷል'' አና ጐሜዝ

Image
አና ጐሜዝ ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር ገንቢና ግልጽ ውይይቶችን አደረግኩ አሉ ከዘጠኝ ዓመት በፊት በተካሄደው የግንቦት 1997ቱ ምርጫ የአውሮፓ ኅብረትን በመወከል የምርጫ ታዛቢ የነበሩት ፖርቱጋላዊቷ አና ጐሜዝ በሰብዓዊ መብት አያያዝ ላይ ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር መነጋገራቸውን ገለጹ፡፡ ዛሬ በሚጠናቀቀው የአፍሪካ፣ የካሪቢያን፣ የፓስፊክና የአውሮፓ ኅብረት የጋራ የፓርላማ 26ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ለመካፈል አዲስ አበባ የመጡት አና ጐሜዝ፣ በአዲስ አበባ በነበራቸው ቆይታ ከኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት ጋር ገንቢና ግልጽ ውይይቶችን ማድረጋቸውን ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ የጋራ ስብሰባው ላይ ለመካፈል ወደ አዲስ አበባ የመጡት የአውሮፓ ኅብረት ፓርላማ አባልና በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ ከፍተኛ ትችት በመሰንዘር የሚታወቁት አና ጐሜዝ፣ ወደ ኢትዮጵያ ለመግባት ምንም ዓይነት የቪዛ ችግር እንዳልገጠማቸው ገልጸው ይህም አዲስ ዓይነት የፖለቲካ አተያይ እየተፈጠረ መሆኑን ያሳያል ብለዋል፡፡ ምንም እንኳን ከጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሕልፈት በኋላ በኢትዮጵያ የተለየ የፖለቲካ አተያይ አለ ያሉት አና ጐሜዝ፣ አጠቃላይ የፖለቲካው ምህዳር ግን ከ1997ቱ ምርጫ ወቅት ከነበረው ጋር ሲነፃፀር የባሰ ነው የሚል አመለካከት አላቸው፡፡ «ከ1997 ምርጫ ቀደም ብሎ ተስፋ ይታይበት የነበረው የኢትዮጵያ ፖለቲካ፣ ምህዳር በምርጫው ምክንያት በተፈጠረው ቀውስ ከምርጫው በፊት ወደነበረበት አስከፊ ሁኔታ ተመልሷል፤» በማለት መንግሥትን ተችተዋል፡፡ ለዚህም እንደ መከራከሪያ የሚያነሱት ከምርጫው በኋላ የወጡትን ሕጐች በምሳሌነት በማቅረብ ነው፡፡ «ከ1997ቱ ምርጫ በኋላ ሁሉም የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች መሪዎችና አባላት መታሰራቸው፣ የሲቪክ ማኅ

«የልፋታችንን ዋጋ አላገኘንም» - ቡና አምራች አርሶ አደሮች « ቡናን በጥራትና በብዛት ማምረት ግድ ነው» - የሲዳማ ዞን ግብይትና ኅብረት ሥራ መምሪያ ኃላፊ

Image
አርሶ አደሮቹ እንደሚናገሩት ቀደም ሲል አንድ ኪሎ እሸት ቡና እስከ  13  ብር ድረስ ሸጠው ነበር፤ አሁን ግን ተመሳሳይ መጠን ያለውን ቡና በአምስት ብር ብቻ ለመሸጥ ተገድደዋል፤ በሲዳማ ዞን ዳሌ ወረዳ የአዋዳ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ነዋሪው አርሶ አደር ተፋዬ ወቴ ከቡና ሌላ በማሳቸው እንስትም በቆሎም ያመርታሉ። ይሁንና ሰፋ ያለው መሬት በቡና የተሸፈነ ነው። ከዚህ መሬት በየዓመቱ የሚያገኙት የገንዘብ መጠን እንደ ቡና ገበያ ዋጋው መለያየቱን ይናገራሉ። እርሳቸው እንደሚሉት ፤ቀደም ባሉት ጊዜያት የቡና ምርታማነት ከፍ ያለ ቢሆንም በመሀል ደግሞ መቀነስ ታይቶበታል። ነገር ግን በአካባቢው ያሉ የግብርና ባለሙያዎች የቡናን ችግኝም ሆነ ዛፍ እንዴት መያዝ እንደሚገባ በሰጡት ትምህርት አሁን ላይ ለውጥ ይታያል። ምርቱ ቢኖርም የገበያ ሁኔታው አሳሳቢ ሆኗል። በተለይ በተጠናቀቀውና በተያዘው ዓመት የቡና ዋጋ ከሚጠበቀው በታች ዝቅ ማለቱን የሚያመለክቱት አርሶ አደር ተስፋዬ ዘንድሮ አንድ ኪሎ እሸት ቡና በአምስት ብር ለመሸጥ መገደዳቸው የልፋታቸውን ዋጋ እንደሚያሳጣቸው ይገልፃሉ። ዋጋው ከፍና ዝቅ የማለቱ ጉዳይም እንዳሳሰባቸው ነው የሚጠቅሱት። « እኛ የምንፈልገው የተጋነነ ትርፍ አይደለም። ከሁለት ዓመት በፊት የነበረው የቡና መሸጫ ዋጋ ከአምናና ከዘንድሮው ይሻል ነበር። ቢያንስ አንዱን ኪሎ እሸት ቡና እስከ  13  ብር ድረስ ሸጠናል። ነገር ግን ትርፍ አጋብሰናል ማለት ሳይሆን ለድካማችን የተሻለ ዋጋ ነበር የሚያስብል ነው። ስለዚህም የክልሉና የዞኑ ቡና ግብይት በዚህ ጉዳይ ላይ ተነጋግረው የልፋታችንን ዋጋ የምናገኝበትን መፍትሄ ቢያመቻቹ መልካም ነው »  ይላሉ አርሶ አደር ተስፋዬ። በአሁኑ ወቅት አንድ ኩንታል ጤፍ በአካባቢው በ 1 ሺ 300 

አምራቹ በቡና ዋጋ መቀነስ እንዳይጎዳ ማድረግ ያስፈልጋል

 ... ይህ በሲዳማ ቡና አምራቾች ላይ የተከሰተው ችግር የቡና ዋጋ በዓለም ገበያ ዋጋ የሚወሰን ከመሆኑ አኳያ የሌሎች ሀገሮች ቡና አምራች አርሶ አደሮችም ችግር ነው። ችግሩ ከቡና ጋር የጠበቀ ግንኙነት ላለውና ቡና ምግቡ፣ ልብሱ፣ መዝናኛው በአጠቃላይ የኑሮው ዋልታና ማገር ለሆነው የኢትዮጵያ ቡና አምራች ምን ያህል አሳሳቢ ሊሆን እንደሚችል በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል። የቡና ዋጋ እየቀነሰ መምጣት በአስቸኳይ የሚፈታ ካልሆነ የቡና አምራቾች የልፋታቸውን ዋጋ ወደ ሚያስገኙላቸው ዘርፎች ፊታቸውን እንዲያዞሩ የሚያስገድድ ሁኔታ እንዲፈጠር ያደርጋል፤ የግብይት ህብረት ሥራ ማህበራትም ይህንኑ ስጋት እያረጋገጡ ናቸው። ሀገሪቱም ከቡና በከፍተኛ ደረጃ የምታገኘውን የውጭ ምንዛሪ እንዲቀንስ የሚያደርግም ይሆናል። ችግሩ በቡና ልማቱና ግብይቱ ሰንሰለት የሚሳተፈውን በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠር ህዝብ ኑሮ እንዲናጋ ያደርጋል። ኢትዮጵያ ለቡና ልማት በሰጠችው ትኩረት በቡና ተክል የተሸፈነው መሬትም ሆነ ምርት በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መጥቷል። ቡና ከሚመረትባቸው ክልሎች በተጨማሪ በአማራና በትግራይ ክልሎች ጭምር ቡናን በማምረት ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግ በሀገር ደረጃ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ነው። ለቡና አምራቾች ወሳኝ ግብዓቶችን በማቅረብ ጭምር ድጋፍ እየተደረገ ነው። አርሶ አደሩ ምርቱን በአቅራቢያው ለሚገኙ የራሱ የህብረት ሥራ ማህበራት እንዲያቀርብ የሚያስችል ሁኔታ በመፈጠሩም ምርቱ የደላሎችና ህገወጥ ነጋዴዎች ያለአግባብ መጠቀሚያ ከመሆን እየዳነ ነው። በአሁኑ ወቅት የቡና ግብይት የሚካሄድባቸው በርካታ የግብይት ማዕከላት ተቋቁመው እየሰሩ ናቸው። በተለይ አርሶ አደሩ ምርቱን ለህብረት ሥራ ማህበራት ማቅረብ በመቻሉ የቡና ዋጋ በሚወድቅበት ወቅት ምርቱን የሚያደ

Round Huts in traditional Sidama Style, Ethiopia

Image
http://www.viewat.org/?i=en&id_pn=23865&sec=pn

ደደቢትና ሀዋሳ ከነማ ተጋጣሚያቸውን አሸነፉ

በኢትዮጵያ ፕሪሜየርሊግ ሶስተኛ ሳምንት መርሀ ግብር እሁድ ህዳር 15/03/2005 ሁለት ቀሪ ጨዋታዎች የተካሄዱ ሲሆን በደቡብ ደርቢ ሀዋሳ ከነማ ሲዳማ ቡናን እንዲሁም  ደደቢት አርባ ምንጭ ከነማን በተመሳሳይ 1ለ0 አሸንፈዋል፡፡ ደደቢት በብሔራዊ ቡድኑ ጨዋታዎች ምክንያት ከሶስት በላይ ተጨዋቾን በማሰመረጡ ከኢትዮጵያ ቡናና  ከሲዳማ ቡና የነበረውን ሁለት የፕሪሜየር ሊግ ጨዋታ ማራዘሙ ይታወሳል፡፡ የመጀመሪያ የሊጉን ጨዋታ ከብሔራዊ ቡድኑ መልስ ከአርባ ምንጭ ጋር ያደረገው የባለፈው ዓመት ሻምፒዮና ደደቢት ፣በዳዊት ፍቃዱ በተገኘች ብቸኛ ጎል የመጀመሪያ የሊጉን ድል ማስመዝገብ ችሏል፡፡ ደደቢት በአጭር የኳስ ፍሰት ጨዋታውን ለመቆጣጠር ያደረገው ሙከራ ሙሉ ሶስት ነጥብ ይዞ እንዲወጣ አስችሎታል፡፡ በደቡብ ደረቢ በሜዳው ሲዳማ ቡናን ያስተናገደው ሀዋሳ ከነማ በበኩሉ በአንዷለም ንጉሴ ወሳኝ ጎል የመጀመሪያ የሊግ ድሉን አስመዝግቧል፡፡ ሀዋሳ ከነማ የመጀመሪያውን ጨዋታ በሜዳው መብራት ሀይልን ቢያሰተናግድም ሽንፍት ማስተናገዱ ይታወሳል፡፡ሲዳማ ቡና በአንጻሩ ሁለቱንም ጨዋታዎች በመሸነፍ ደካማ አጀማምር አሳይቷል፡፡ ሊጉን መከላከያ በሶስት ጨዋታ 7 ነጥብ ሰብስቦ መምራት ሲችል፣ ሙገር ሲሚንቶ በሁለት ጨዋታ 6 ነጥብ በመያዝ ሁለተኛ እንዲሁም ወላይታ ዲቻ በተመሳሳይ ሁለት ጨዋታ 4 ነጥብ በመያዝ ከ1 እስክ 3 በመምራት ላይ ይገኛሉ፡፡

Etiopia, diario di viaggio fuori dalle rotte turistiche

Image
Piu' informazioni su: etiopia Arrivati ad  Addis Abeba  quasi ci si vergogna per le imprese non certo gloriose degli italiani alcuni decenni fa proprio in quei luoghi. Un amico ci porta a mangiare in un ristorante dove abbiamo il primo approccio con la  n'jera , piatto tipico (ed è anche l'unico) che poi ci sarà servito ogni giorno, a pranzo e a cena. Somiglia ad una grande crepe, è di forma circolare e su di essa vengono versati dei condimenti, come legumi, pezzetti di carne o pesce, salsine varie, verdure, tutto molto pepato. Si ritaglia poi con le mani, si raccoglie del condimento facendone un boccone che si introduce in bocca sempre rigorosamente con le mani. Se si vuole si può richiedere anche del pane, che è piuttosto buono. L'indomani da Addis ci trasferiamo con dei fuoristrada (i mezzi migliori per viaggiare in Africa dove le strade sono quasi sempre in terra) a  Shashamene;  stiamo attraversando la  Rift Valley . Francesca ci spiega che nell

Exotic Origins Coffee and Common River.Org come together in collaboration for Ethiopia’s Aleta Wondo coffee growing community.

Image
Ethiopia’s Common River Making a Difference with Exotic Origins Coffee Company Marin County, California (PRWEB) November 22, 2013 Exotic Origins Coffee began in origin around the globe, tracing and sourcing extraordinary, rare 88+ rated and above single limited harvests in order to offer a “deeper experience for the adventurous palate” . Common River.Org  is a multi-faceted development organization improving lives of women and children in the Sidama region of Ethiopia, coffee’s birthplace. Donna Sillan , Co-founder met with Scott Plail; Founder & CEO, Priscilla Broward; VP Sales & Marketing and Willem Boot, International Coffee Expert & VP Global Procurement for Exotic Origins Coffee in August 2013 to discuss the journey ahead and identify ways to begin small micro scale enterprises for the local women. Common River’s roots are deep due to Tsegaye Bekele’s (Co-founder) family in Ethiopia, and already proven success. Their organization built a school for edu

“ለዜጐቻችን ስቃይ የሳኡዲና የአገራችን መንግስታት ተጠያቂ ናቸው” ተቃዋሚ ፓርቲዎች

ሠሞኑን በሳውዲ አረቢያ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ላይ እየደረሠ ያለው ግፍና ስቃይ እንዳሳዘናቸው የገለፁ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች፤ የሣውዲ አረቢያ መንግስት እና የኢትዮጵያ መንግስት የመጀመሪያ ደረጃ ተጠያቂ ናቸው ሲሉ ተናገሩ፡፡ የመድረክ ሊቀመንበር ዶ/ር መራራ ጉዲና፣ ሣውዲ አረቢያ የራሷንም ዜጐች መብት የማታከብር ሃገር መሆኗን ገልፀው፣ በኢትዮጵያውያን ላይ የተፈፀመው አሠቃቂ ስራ ግን በ21ኛው ክ/ዘመን የማይጠበቅ ግፍ ነው ብለዋል። በተለይ በሴቶች ላይ የሚፈፀመው ድርጊት አስነዋሪ ነው በማለት መወገዝ እንዳለበት የተናገሩት ዶ/ር መራራ፤ ዋናው ተጠያቂ የሳውዲ መንግስት ነው ብለዋል፡፡ “በሌላ በኩል ኢህአዴግ ሃገሪቱን የስደት ሃገር አድርጓል” ያሉት ዶ/ር መረራ፤ በሜድትራኒያን፣ በየመንና በደቡብ አፍሪካ መስመሮች የሚሰደዱ ዜጐቻችን የአውሬ ሲሣይ እየሆኑ ነው፤ በሃገር ውስጥም በውጭም የዜጐቹን መብት ማስከበር ያልቻለው የኢትዮጵያ መንግስት ተጠያቂ መሆን አለበት” ብለዋል፡፡ በሣውዲ አረቢያ ኢትዮጵያውያን ላይ እየተፈፀመ ያለውን ግፍ በትኩረት እየተከታተሉ መሆናቸውን የሚገልፁት የመኢአድ ፕሬዚዳንት አቶ አበባው መሃሪ በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ መንግስት በዜጐቻችን ላይ የተፈፀመውን ድርጊት ለመከላከልና ለማስቆም አለመቻሉ መንግስት አልባ መሆናችንን የሚያሣይ ነው ብለዋል፡፡ አቶ አበባው እንደሚሉት፤ የሌላ ሃገር መንግስት ቢሆን ኖሮ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩን እዚያ ሃገር ድረስ ልኮ ሄዶ የዜጐቹን መብት ያስከብር ነበር ብለዋል - አቶ አበባው፡፡ እዚህ ሃገር የውጭ ዜጐች ከቀን ሠራተኛነት ጀምሮ በተለያዩ የስራ መስኮች ላይ መብታቸው ተከብሮላቸው ይኖራሉ ያሉት አቶ አበባው፤ “የኛ ዜጐች በሳውዲ ከሰውነት በታች ተዋርደው ግፍ የሚደርስባቸው ለዜጐች የሚቆረቆር መንግስት ስለሌ

የቀድሞ ሲዳማ ልማት ኮርፕሬሽን (SDC) እህት የልማት ድርጅቶች የት ደረሱ?

Image
የሲዳማ ዞን መንግስት በቀድሞ የሲዳማ ልማት ኮርፕሬሽን እህት የልማት ድርጅቶች ላይ በያዘው የተሳሳተ ኣቋም ድርጅቶቹን ኣጠናክሮ ለታለሙለት ኣላማ እንድውሉ እና ስፊውን የሲዳማን ህዝብ እንድጠቅሙ ከማድረግ ይልቅ ድርጅቶቹን እንደጠላት ንብረት በማየት የሚጠፉበትን እና የሚበተኑበትን ሁኔታዎችን ብቻ በማመቻቸት ላይ የተጠመዷል የሲዳማ ማክሮ ፋይናንስ የመንግስት ድጋፍ ያስፈልገዋል ክፍል ሁለት የሲዳማ ማክሮ ፋይናንስ ተቋም (SMFI) በኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ የስራ ፋቃድ ኣግኝቶ በራሱ ቦርድ የሚተዳደር የገንዘብ ተቋም ነው።ተቋሙ በከተሞች ኣካባቢ ቤትን እና ሌሎች ንብረቶችን በመያዝ ብድር የመስጠት ኣገልግሎት በመስጠት ላይ ሲሆን፤ እንደሌሎች መሰል የኣገሪቱ የብድር እና የቁጠባ ተቋማት ሁሉ ሰዎች በቡድን ተደራጅተው ገንዘብ የሚበደሩበትን መንገዶች በማመቻቸት ኣገልግሎት ይሰጣል። በኣገልግሎቱም እስከ ሃምሳ ሺ ነው የሚያበድር ሲሆን በግለሰብ ደረጃ ግን ከሶስት ሺ ብር በላይ ኣያበድርም። ለነገሩ በኣሁኑ ወቅት በኣገሪቱ ባለው የኑሮ ውድነት ብድሩን የሚወስዱ ሰዎች በሶስት ሺ ብር ምን ኣይነት ኢንቨስትመንት ልያደርጉ እንደምችሉ ግልጽ ባይሆንም ብዙዎቹ በገንዘብ ኣያያዝ ላይ ትምህርት ሳይሰጣቸው የብድሩ ተጠቃሚ ስለምሆኑ የተበደሩትን ገንዘብ ላላለሙለት ጉዳይ ላይ በማዋል እዳ ውስጥ ስገቡ ታይተዋል። ሰዎች የተበረሩትን ገንዘብ በውቅቱ ኣለመመለሳቸው ከብድር እና ቁጠባ ተቋሙ ጋር እንድካሰሱ ምክንያት ሆኗል። ጉዳዮቻቸው በፍርድ ቤቶች እየታየ ያሉ እና ቤት ንብረቶቻቸውን ሽጠው ለመክፈል የተገደዱ ብዙዎች ናቸው። ለማንኛውን ተቋሙ በኣሁኑ ጊዜ የብድር እና የቁጠባ ኣገልግሎትን በተዳከመ መልኩ በመስራት ላይ ይገኛል። ለሲዳማ ማክሮ ፋይናንስ

የቀድሞ ሲዳማ ልማት ኮርፕሬሽን (SDC) እህት የልማት ድርጅቶች የት ደረሱ?

Image
ለሲዳማ ህዝብ ልማት እና ብልጽግና እንዲያመጡ ተብለው የተቋቋሙ የቀድሞ የሲዳማ ልማት ኮርፕሬሽን (SDC) እህት የልማት ድርጅቶች በዞኑ መንግስት ትኩረት በመነፈጋቸው የተነሳ ፈርስዋል፤ በመፍረስም ላይ ናቸው የሲዳማ ልማት ኮርፕሬሽን (SDC) ፦ ለ ሲዳማ ህዝብ የልማት ስራዎች ለመስራት ቀርቶ ድርጅቱ በራሱ በሁለት እግሩ መቆም ኣልቻለም ፉራ ኮሌጅ፦ ከምመለከተው ኣካል ትኩረት በመነፈጉ የተነሳ ባጋጠመው የትምህርት ጥራት ጉድለት ኣብዛኛዎቹን የትምህርት ክፍሎች በመዝጋት ላይ ያለ ኮሌጅ ሆኗል ሬድዮ ሲዳማ፦ ከተቋቋመበት ዓላማ ውጭ ለመንግስት የፖለቲካ ማካሄጃነት በመዋል ላይ ያለ ጋራምባ ኮንስትራክሽ እና ኣዳሬ ኢንጅኔሪንግ፦ ተበትነው እና ፈርሰው ታሪክ የሆኑ ሲዳማ ማክሮፋይናስ፦ በኦሞ ማክሮፋይናንስ የታፈነ ክፍል ኣንድ ኤስዲስ በኣይርሽ መንግስት የገንዘብ ድጋፍ የተቋቋመ እና በሲዳማ ውስጥ በርካታ የልማት ተግባራትን ስያከናውን የቆየ ድርጅት ነው። ይሄው ድርጅት በወቅቱ በርካታ እህት ድርጅቶችን በስሩ ኣቋቁሞ ይስራ የነበረ ሲሆን ካቋቋማቸው ድርጅቶች መካከል በኣሁኑ ጊዜ ኣብዛኛዎቹ ከተቋቋሙበት ዓላማ ውጭ በማገልግል ላይ ናቸው፤ የቀሩት ደግሞ ፍርስዋል። እንደ ሪፖርተራችን ጥቻ ወራና ዘገባ ከሆነ፦ ከሲዳማ ልማት ፕሮግራምነት ወደ ሲዳማ ልማት ኮርፕሬሽነትን የተቀየረው SDC ፤ በወቅቱ የሲዳማ ህዝብ ኩራት ሆኖ ለሲዳማ ህዝብ ልማት የምቆረቆሩ ግለሰቦች እንደንብ የምሯሯጡበት የነበረ ሲሆን፤ በኃላ ላይ በመንግስት ጠልቃ ገቢነት የተነሳ የስራ ኣቅሙ የተመታ እና የላሸቀ ድርጅት ነው። ድርጅቱ በኣሁኑ ወቅት ስፋፊ የእርሻ መሬት በኮንትራት መልክ በመያዝ በተለይ በቆሎን በመዝራት ስራ ላይ የተሰማራ ድርጅት ነ

Europe tries new recipe to combat hunger in Ethiopia

SPECIAL REPORT  / Learning from past crises, the European Commission has changed tack on its approach to food security in the Horn of Africa, focusing on resilience to droughts and supporting diversification in local farming production. The list of hunger catastrophes in the history of the Horn of Africa is long. The latest one, only two years ago, was triggered by an extreme drought. Such extreme weather events are only expected to become more frequent with climate change, making preparedness more crucial than ever. Anticipating those changes, the EU is trying to help affected countries deal with emergency situations. Last October, the European Commission sent an additional €50 million in aid to the southern and eastern regions of Ethiopia as part of its Supporting Horn of Africa Resilience (SHARE)  programme. The plan, presented jointly by EU Development Commissioner Andris Piebalgs and EU Commissioner for Humanitarian Aid Kristalina Georgieva, was intended to strength