Posts

Showing posts from January, 2017

MBA students help Ethiopia tackle the impact of urbanisation

For Ria Tobaccowala, a Chicago native studying in New York, arriving in the fast-growing southern Ethiopian city of Hawassa was a revelation. “The first plants are going up, the first airport is being constructed and the first non-dirt roads are being built,” she says. “Seeing how that’s impacting people’s lives was eye-opening.” Tobaccowala, who is studying for a dual MBA/MFA (Master of Fine Arts) degree at New York University, had spent the previous three months working with four classmates on a strategic plan to protect a swath of land in Hawassa, 175 miles south of Addis Ababa, the capital. Their objective was to shield Hawassa’s lake from dangerous pollutants, create a public park and bolster local infrastructure to support the city’s expansion. When the team arrived in April, Tobaccowala and her teammates had just a week to finish their proposal before sharing their ideas with Pewodros Gebiba, the city’s mayor. The group’s biggest priority, though, was to “get an unders

‹‹የአገር ውስጥና የዓለም አቀፍ ገበያ አለመናበብ ለአገሪቱ የቡና ኤክስፖርት ንግድ አለማደግ አንዱ ምክንያት ነው››

Image
ሪፖርተር ፡- ለቡና የውጭ ገበያ ከሚከፍለው ዋጋ የኢትዮጵያ አምራቾች ምን ያህል ይደርሳቸዋል? አቶ ሳኒ ፡- ከ35 እስከ 40 በመቶ ቢሆን ነው፡፡  ሌላው በሙሉ ከአርሶ አደሩ በላይ ያሉት የግብይት ሰንሰለቱ ተሳታፊ አካላት የሚቀራመቱት ነው፡፡ ዋናውን ለግብርና (ለቡና) ልማት ዕድገትም ሆነ ለቀጣይነት አርሶ አደሩ ትልቅ ድርሻ የሚገባውና የተጠቃሚነቱን ድርሻ መውሰድ የሚገባው አርሶ አደሩ ነበር፡፡ ስለዚህ ከፍትሐዊነት አንፃር ብዙ መሠራት የሚጠብቀው ነው፡፡ ሌላው በዘመናዊ የግብይት ሥርዓት በግብዓት ተዋንያን ዘንድ መተማመን መፈጠር አለበት፡፡ እርስ በርስ መተሳሰብ መኖር አለበት፡፡ በእኛ ሁኔታ ሲታይ የቡና ዘርፍ ለበርካታ ሕገወጥ ንግድና ዝውውር የተጋለጠ ነው፡፡ ይኼም የሆነበት ምክንያት ወጥ በሆነ መንገድ ሒደቱን ተከታትሎ ራሱን ችሎ የሚመራ ተቋም ባለመኖሩ ነው፡፡ ይህ ምክንያት ታምኖበት ቡናና  ሻይ ባለሥልጣን ተደራጅቷል፡፡ እንግዲህ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ሲደራጅ የግብይት ሥርዓቱንም የመገንባት ተልዕኮ ወስዷል ማለት ነው፡፡ ሦስተኛ እሴት ለሚጨምሩ ኢንዱስትሪዎች የግብርና ምርቶችን ማምረት ብቻ ተጠቃሚ አያደርግም፡፡ እሴት ጨምሮ በተሻለ ዋጋ በመሸጥ የዘርፉ ተዋንያንን ተጠቃሚ ማድረግ ይገባል፡፡ አገሪቷንም ተጠቃሚ ማድረግ ይገባል፡፡ ይህንን ሥራ በማከናወን ሒደት ላይ አሁን ያሉት ተቋማት አሉ? የሉም? ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ይህንን ሁሉ ተልዕኮ ይወስዳል? አይወስድም የሚለው ጥያቄ ይደመጣል፡፡ ቀድሞ የነበሩት ተቋማት አሉ፡፡ በጋራ እየሠራን ነው፡፡ እነዚህን ሥራዎች የሚሠሩ ተቋማት ተጠሪነታቸው በሚኒስቴር ደረጃ ለሦስት አካላት ነው፡፡ ለእርሻና ተፈጥሮ ሀብት ሚኒስቴር፣ ለንግድ ሚኒስቴርና ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ነው፡፡ እነዚህን ተቋማት ለማቀናጀት የሚ

የእንግሊዝ ዓለም አቀፍ ልማት ሚኒስትር ሐዋሳ የኢንዱስትሪ ፓርክን ሊጎበኙ ነው

Image
የኛ ለተባለው ፕሮጀክት የሬዲዮ ፕሮግራም ይለቀቅ የነበረው ፈንድ እንዲቋረጥ የወሰኑት የእንግሊዝ ዓለም አቀፍ ልማት ሚኒስትር ኢትዮጵያን ሊጎበኙ ነው፡፡ ከያዟቸው የጉብኝት ዕቅዶች መካከል ሐዋሳ የኢንዱስትሪ ፓርክ እንደሚገኝበት የሪፖርተር ምንጮች ገልጸዋል፡፡ የእንግሊዝ ዓለም አቀፍ ልማት ሚኒስትሯ ፕሪቲ ፓቴል የኛ ለተባለው የሬዲዮ ፕሮግራም ይለቀቅ የነበረው 5.2 ሚሊዮን ፓውንድ እንዲቋረጥ ያደረጉት በቅርቡ መሆኑ ይታወሳል፡፡ ሚኒስትሯ ፈንዱ ያቋረጠበት ምክንያት መንግሥታቸው ከዕርዳታ የተለየ መንገድን እንደሚመርጥና ይህም ዓለም አቀፍ የንግድ ትብብርን ማበረታት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ የኛ ለተባለው የሬዲዮ ፕሮግራም ፈንድ እንዲቋረጥ ካደረጉ በኋላ የሐዋሳ የኢንዱትሪ ፓርክን በዚህ ሳምንት እንደሚጎበኙ ታውቋል፡፡ ሚኒስትሯ የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔን እንደሚከታተሉ፣ ከጉባዔው ጎን ለጎን ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝንና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩን ዶ/ር ወርቅነህ ገበየውን በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ እንደሚያነጋግሩ የሪፖርተር ምንጮች ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ ከፓኪስታን ቀጥሎ ትልቁን የእንግሊዝ ዕርዳታ የምታገኝ ሲሆን፣ እ.ኤ.አ. በ2015 ብቻ 334 ሚሊዮን ዶላር ማግኘቷን መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ Source