Posts

በሲዳማ ዞን በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወሩ የነበሩ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች መያዛቸው ተገለጸ

Image
በደቡብ ክልል በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወሩ የነበሩ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ (ኤፍ.ቢ.ሲ) በደቡብ ክልል በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወሩ የነበሩ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገለፀ። በቁጥጥር ስር የዋሉትም 10 የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች፣ ሁለት ቦምቦች እና 600 ጥይቶች ናቸው። ከዚህ በተጨማሪም 3 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር የሚያወጣ ቡና በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገልጿል። ፎቶ ከ ደህረ ገጽ የደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል መረጃ ኢንተለጀንስ ዳይሬክተር ኮማንደር ጉራማይሌ ጉራኦ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደተናገሩት፥ የክልሉ ፖሊስ ባደረገው ክትትል ነው መሳሪያዎቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት። የጦር መሳሪያዎቹ በህገ ወጥ መንገድ ከደቡብ ሱዳን ጠረፍ የገቡና በሲዳማ ዞን ሲዘዋወሩ በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም ኮማንደር ጉራማይሌ ገልፀዋል። በተጨማሪም በቤንች ማጂ ዞን በከፋ እና በሸካ ዞኖች በ10 አይሱዙ ተሽከርካሪዎች ተጭኖ፥ በህገ ወጥ መንገድ በመዘዋወር ላይ የነበረ 3 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር የሚገመት ቡና  በቁጥጥር ስር ውሎ ለመንግስት ገቢ መደረጉን አስታውቀዋል። ቡናውን ጭነው የነበሩ 12 አሽከርካሪዎች እና ረዳቶች ጉዳያቸው በህግ እየተጣራ እንደሚገኝም ኮማንደር ጉራማይሌ አስታውቀዋል። እንደ ኮማንደር ጉራማይሌ ገለጻ፥ በሩብ ዓመቱ በክልሉ ከ4 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ ቶርሽን ጫማዎች፣ የሞተር ሳይክል እና የመኪና ሞተር መለዋወጫዎች፣ የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎች እንዲሁም አዲስና ልባሽ ጨርቆች መያዛቸውን ተናግረዋል። የኮንትሮባንድ እቃውን ጭነው በህገ ወጥ መንገድ ሲያጓጉዙ የነበሩ አሽከርካሪዎችም በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ነው ኮማንደር ጉራማይሌ የገለፁት።

በሰራ ለሚያምነው የሲዳማ ህዝብ ከዚህም በላይ ይባልለታል!

Image
በሰራ ለሚያምነው የሲዳማ ህዝብ ከዚህም በላይ ይባልለታል! የኣበራ ቶሸ የሲዳማን ህዝብ የሰራ ባህል በማሞገስ የተቀኘላቸው ዜማ

ሰሞኑን ከኦሮሚያ ክልል ባሌ ጎባ ዞን የተፈናቀሉት ቁጥራቸው ከኣምስት ሺህ በላይ የሚሆኑ የሲዳማ ተወላጆች በምግብ እና በመጠለያ እጦት ተቸግረዋል

Image
  ሰሞኑን ከኦሮሚያ ክልል ባሌ ጎባ ዞን የተፈናቀሉት ቁጥራቸው ከኣምስት ሺህ በላይ የሚሆኑ የሲዳማ ተወላጆች በምግብ እና በመጠለያ እጦት ተቸግረዋል። ፎቶ ለዝርዝር ወሬውን እዚህ ይጫኑ

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት አያያዝ እንዲስተካከል እንግሊዝ ጥያቄ አቀረበች

Image
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኢትዮጵያ እየተከሰተ ካለው ቀውስ ጋር ተያይዞ እየተፈጠሩ ያሉ የሰብዓዊ መብት አያያዝ ችግሮች እንዲስተካከሉ እንግሊዝ ጠየቀች፡፡   የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሒሩት ዘመነ ከእንግሊዝ አምባሳደር ሱዛና ሞርሄድና ከኤምባሲው የሥራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት ባደረጉበት ወቅት ባለፉት ሁለት ዓመታት በአገሪቱ እየተከሰተ ካለው ቀውስ ጋር ተያይዞ የሰብዓዊ መብት አያያዝ ችግር እንዳለ፣ ኢትዮጵያም ይህን ችግር እንድታስተካክል እንግሊዝ ምክረ ሐሳብ ማቅረቧ ታውቋል፡፡ ይህ ምክረ ሐሳብ የቀረበው ኢትዮጵያና እንግሊዝ ለአራተኛ ጊዜ በሰብዓዊ መብቶች ላይ ያተኮረ የጋራ ውይይት፣ ሰኞ ኅዳር 4 ቀን 2010 ዓ.ም. በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በተካሄደበት ወቅት ነው፡፡ በውይይቱ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሒሩት ዘመነ፣ በኢትዮጵያ የስደተኛና ከስደት ተመላሽ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ተወካዮች፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ተወካዮች፣ በኢትዮጵያ የእንግሊዝ አምባሳደር ሱዛና ሞርሄድና የኤምባሲው የሥራ ኃላፊዎች፣ የብሪታኒያ ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት (ዲኤፍአይዲ) ዳይሬክተሮችና ሌሎች የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ተገኝተው ነበር፡፡ የውይይቱ አጀንዳዎችም የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት አያያዝ፣ ስደት፣ የመንግሥት ተጠያቂነትና ግልጽነት ነበሩ፡፡ የሁለቱ አገሮች የጋራ ውይይት የተካሄደው በዝግ ቢሆንም፣ የሪፖርተር ምንጮች እንደጠቆሙት በኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት አያያዝ ላይ ያሉ ችግሮችን የእንግሊዝ መንግሥት ተወካዮች በዝርዝር አውስተዋል፡፡ አንድ የእንግሊዝ ዲፕሎማት ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ ስደተኞችን በማስተናገድ ግንባር ቀደም አገር ብትሆንም በሰብዓዊ መብት አያያዝ ላይ ችግሮች አሉባት፡፡ ‹‹ይህንን ያህል የስደተኛ

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላት ለታላቁ የህዳሴ ግድብ ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ አደረጉ

Image
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ እስኪጠናቀቅ ከቦንድ ግዥ በተጨማሪ በምርምር ስራ አስፈላጊውን ሙያዊ ድጋፍ ለማድረግ መዘጋጀቱን የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ፡፡ የህዳሴ ግድቡን ዋንጫ አቀባበል ምክንያት በማድረግ የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች፣ መምህራንና ሰራተኞች ለግድቡ ግንባታ ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ አድርገዋል፡፡ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት አቶ አያኖ በራሶ ዛሬ ለኢዜአ እንደገለጹት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ እስኪጠናቀቅ የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ድጋፉን አጠናክሮ ለመቀጠል ቃል ገብቷል፡፡ የህዳሴ ግድቡ ግንባታ የመሰረት ድንጋይ ከተጣለበት ጊዜ አንስቶ በቦንድ ግዥ፣ በዕውቀትና በክልሉ በግድቡ ዙሪያ በሚደረጉ የውይይት መድረኮች የተቋሙ ምሁራን ሙያዊ ማብራሪያ በመስጠት ድጋፍ ሲያደርጉ መቆየታቸውን ተናግረዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው በምርምር ረገድም ራሱን የቻለ የውሀ ዘርፍ እንዳለው ጠቁመው በቀጣይም የአባይ ውሀ ሀገሪቱ የበለጠ መጠቀም የምትችልበትን ሁኔታን በጥናት በመለየት አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን አቶ አያኖ ገልጸዋል፡፡ የህዳሴ ግድቡ ዋንጫ ሀዋሳ መግባቱን ተከትሎ የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች፣ መምህራንና ሰራተኞች በስጦታና በቦንድ ግዥ ከ30 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጋቸውንም አመልክተዋል፡፡ በግላቸው ለሶስተኛ ጊዜ በወር ደመወዛቸው የቦንድ ግዥ መፈጸማቸውንም ጠቁመዋል፡፡ በዩኒቨርሲቲው የኬሚስትሪ የትምህርት መስክ የሶስተኛ ዓመት ተማሪ ዮርዳኖስ ገብረስላሴ በበኩሏ የአባይ ወንዝ ለሀገሩ ጥቅም እንዲሰጥ የግድቡ መገንባት የሚኖረው ፋይዳ ከፍተኛ እንደሆነ ጠቅሳ የታላቁ የህዳሴ ግድብ ዋንጫ ወደ ዩኒቨርሲቲው መምጣቱ እንዳስደሰታት ተናግራለች፡፡ የኮምፒውተር ሳይንስ የአራተኛ ዓመት ተማሪው  ታደሰ አይጠገብ በሰጠው አስተ