የሲዳማ ብሄር ዘመን መለወጫ ፊቼ መከበር ጀመረ
የሲዳማ ብሄር ዘመን መለወጫ ፊቼ በዓል ዛሬ መከበር ጀምሯል፡፡ በሲዳማ ባህል አዳራሽ በተካሄደ ሲምፖዚየም ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ ደሴ ዳልኬ የበዓሉን እሴቶች ከዘመን ዘመን በማሸጋገር ለአለም ቅርስነት እንዲበቃ ላደረጉ የሃገር ሽማግሌዎች ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ "የሲዳማ ብሄር የዘመን መለወጫ ፊቼ በአለም ቅርስነት መመዝገቡ የክልሉን ብሔሮች ብሔረሶቦችና ህዝቦች አንድነት የሚያጠናክር ነው "ብለዋል፡፡ የብሔሮች ብሔረሶቦችን ማንነት የሚያስከብር ስርዓት በመገንባቱ ባህሎቻቸው በአደባባይ እንዲከበሩ እድል መፈጠሩንም አቶ ደሴ ገልጸዋል፡፡ የበዓላቱ መከበር ለተጀመረው ልማትና ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ወሳኝ በመሆኑ በዓሉን ከማክበር ባሻገር የተግባር አጀንዳ ማድረግ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡ ለደንና ለተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ፣ የመቻቻልና የመከባበር እሴቶች እንዲጎለብቱ ወጣቶች የድርሻቸወን መወጣት እንዳለባቸውም አመልክተዋል፡፡ ዛሬ የተጀመው የፊቼ በዓል ነገም በጉዳማሌ አደባባይና በተለያዩ ወረዳዎች የሚቀጥል በመሆኑ ባህላዊ እሴቱን በጠበቀ መልኩ እንዲከበር የሃገር ሽማግሌዎች ሃላፊነት እንዳለባቸውም ተመልክቷል፡፡ በዓሉ በአለም ቅርስነት እንዲመዘገብ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ተቋማትና ግለሰቦች ርዕሰ መስተዳድሩ አመስግነዋል፡፡ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሃመድ በበኩላቸው "ቅርሶች የማንነታችን መገለጫ በመሆናቸው በማንኛውም ጊዜና ቦታ ተገቢው እንክብካቤና ጥበቃ ሊደረግላቸው ይገባል" ብለዋል፡፡ የሲዳማ ብሄርም ለዘመናት ጠብቆ ለዚህ ትውልድ እንዲበቃ ያደረገው ፊቼ ጨምባላላ በማይዳሰሱ ቅርሶች በመመዝገቡ ሃገሪቱን ቀደምት የቅርስ ባለጸጋ አድርጓታል፡፡ የቅ