የሲዳማ ቡና የህብረት ስራ ኣምራቾች ምን ይላሉ?
በሲዳማ ዞን ፌሮና አከባቢ ገበሬዎች ሁሌ-ገብ የህብረት ስራ ማህበር ሊቀመንበር አቶ ደስታ መኩካ እንዳሉት ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ከመንግስትና ባለድርሻ አካላት በሚደረግላቸዉ ድጋፍ የማህበራቸው ኢኮኖሚ በከፍተኛ ሁኔታ አድጓል፡፡ ማህበሩ በ1968 የተመሰረተው በ53 አባላትና 43ሺህ ብር ካፒታል እንደነበር አስታውቀው በአሁኑ ወቅትአራት ሺህ 735 አባላት፣ከ28 ሚሊዮን ብር የሚበልጥ ካፒታል ላይ መድረሱን ተናግረዋል፡፡[...] ማህበሩ ከአባልና ሌሎችም ቡና ተረክቦ በተመጣጣኝ ዋጋ በመሸጥ አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ ትኩረት መሰጠቱን በመጠቆም ባለፈዉ በጀት ዓመት ብቻ ለማዕከላዊ ገበያ ካቀረበዉ ደረቅና የታጠበ ቡና 12 ነጥብ ስድስት ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን ተናግረዋል፡፡ [...]የሲዳማ ኤልቶ ገበሬዎች ህብረት ስራ ዩኒየን ስራ አስኪያጅ አቶ ሲሳይ ዮሀንስ ህብረት ስራ ማህበራት የአባሎቻቸውን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከመንግስት የሚደረግላቸዉ እገዛ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማበርከቱን ተናግረዋል፡፡ ዩኒየኑ በ1996 ዓ.ም በሰባት ማህበራትና 67 ሺህ መነሻ ካፒታል መመሰረቱን የተናገሩት ስራ አስኪያጁ አባል ማህበራት 89፣ካፒታላቸው ከ16 ሚሊዮን ብር በላይ መድረሱን ገልፀዋል፡፡ ዩኒየኑ የአከባቢዉን ስነ ምህዳር መሰረት ዘመናዊ የምርት ማሳደጊያ ግብዓት በማቅረብ ምርትና ምርታማነት የመጨመር ስራ ላይ ትኩረት መሰጠቱን ገልጸው የእንስሳት መኖ በማዘጋጀት ለአርሶ አደሩ በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ላይ እንደሚገኝም አስታውቀዋል፡፡ የሲዳማ ቡና አብቃይ ገበሬዎች ህብረት ስራ ዩኒየን ቁጥጥር ኮሚቴ ሀላፊ አቶ ማሞ ለማ ፌሮና አከባቢ ህብረት ስራ ማህበር የአባሎቹንና የአከባቢዉን ህብረተሰብ ችግር ከማስወገድ ባሻገር ለሌሎች ማህበራት የቁሳቁስ፣ የ