Posts

ሀዋሳ 5ኛውን የመላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች ታዘጋጃለች

Image
ግንባታው እየተጠናቀቀ ያለውና 40 ሺ ሰዎችን መያዝ የሚችለው የሀዋሳ ስታዲየም የውድድሩ ድምቀት እንደሚሆን ይጠበቃል፤ 8 ኛው የፌዴራል ስፖርት ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ከትናንት በስቲያ በተጠናቀቀበት ወቅት በ 2008 ዓም የሚካሄደውን የ 5 ኛውን መላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች እቅድ ሰነድ አጽድቋል። ውድድሩን የሀዋሳ ከተማ ታስተናግዳለች። ጉባኤው ሰነዱን ያጸደቀው ከትናንት በስቲያ በተናቀቀበት ወቅት ነው። በ 1999 ዓም የተጀመረውና ሁሉንም ክልሎች ባሳተፈ መልኩ የሚካሄደው የመላ አፍሪካ ጨዋታዎች የኦሎምፒክን ጽንሰ ሃሳብን ይከተላል። በየሁለት ዓመቱ የሚዘጋጀው ይህ ውድድር ብዛት ባለው የስፖርት ዓይነት ብዛት ያላቸውን ስፖርተኞች በማሳተፍም ይታወቃል። በ 2008 ዓ . ም የሚካሄደው የ 5 ኛው መላ ኢትዮጵያ ጨዋታም በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል በሃዋሳ ከተማ የሚዘጋጅ ይሆናል። የጨዋታው እቅድ ሰነድም በፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን የስፖርት ተሳትፎና ውድድር ፌስቲቫል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ በቀለ ቀርቧል። በዕቅዱም ላይ በሃዋሳ ከተማ በሚዘጋጀው ውድድር ተጫዋቾችን፣ አሰልጣኞችን፣ የቡድን መሪዎችንና ሌሎችንም ጨምሮ 4 ሺ 150 የሚሆኑ የልኡካን ቡድን አባላት ይሳተፉበታል ተብሎ ይጠበቃል። በዚህም መሰረት ከጥር 1 እስከ መጋቢት 30 ቀን 2008 ዓ . ም ድረስ ክልሎች ዝግጅታቸውንና የተጫዋቾች መረጣቸውን እንደሚጨርሱ በእቅዱ ላይ ተገልጿል። በዚህም መሰረት የክልሉ መንግስት ባለፈው ዓመት አዘጋጅ ከነበረው የኦሮሚያ ክልል መልካም ተሞክሮዎችን እንዳገኘ ተገልጿል። ክልሉ ለውድድሩ ማካሄጃ የሚያውላቸው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ዝግጅት ከወዲሁ ተጀምሯል። አዲሱ የሃዋሳ ከተማ ስታዲየም፣ የደቡብ ክልል ፖሊስ ሜዳ እንዲሁም

ጉዞ ወደ ጥበበኞቹ አገር

Image
በዘንድሮው በዓል አዛውንቶች ( አያንቱዎች ) የበዓሉ ድምቀት ሆነው ሰንብተዋል፤ በአንድ አገር ውስጥ ማህበረሰባዊ የተቋም ሽግግር እንዲመጣ፣ የህዝቦች የጋራ እሴት እንዲጎለብት እና የትውልድ ቅብብሎሽ መኖር መሰረታዊ ስለመሆኑ የሚያጠያይቅ አይደለም። ሀገር ያለ ሰው አይደምቅም። ሰውም ያለ ሀገር አይፈጠርም። ለሀገር ዘመን ተሻጋሪ ድርና ማጉ ህዝብ ነው። የአንድ ህዝብ ታሪክ መሰረቱ የተከታታይ ትውልዶች ሥራ ነው። እያንዳንዱ ትውልድ ማህበራዊ አንድነቱንና አብሮ የመኖር ህልውናው አረጋግጦ ለሚቀጥለው ትውልድ የሚያስተላልፈው እሴት የዛ ህዝብ የማንነት መገለጫ ነው። የአንድ ህዝብ አገር በቀል እውቀት፣ ልምድ፣ ትውፊታዊ እምነት፣ ወግና ስርዓት፣ ያለፉትን ተከታታይ ትውልዶች ከዛሬው ከወደፊቱ ትውልዶች ጋር የሚያገናኝ፣ የሚያስተዋውቅና የሚያስተሳስር ሰንሰለት ነው። ያ ህዝብ የራሱን የኑሮ ዘይቤ በመደንገግና በመቅረፅ ሥርዓት ባለው መልኩ ህይወቱን ለመምራት ያደረጋቸው የለውጥ ሂደቶች የስብዕናው መገለጫዎችም ሆነው ይስተዋላሉ። ጉዞአችን በደቡብ ምስራቅ አቅጣጫ ነው። የሲዳማ ህዝብ በደቡብ ክልል ከሚገኙ ብሄር ብሄረሰቦች ህዝቦች መካከል አንዱ ነው። ዞኑ በሰሜን ምስራቅና በደቡብ ምስራቅ ኦሮሚያ ክልል እንዲሁም በስተምዕራብ የወላይታ ዞን ያዋስኑታል። የሲዳማ ህዝብ የራሱ የሆነ ቋንቋ ፣ የዘመን አቆጣጠር፣ ባህል፣ ስርዓት፣ ትውፊት፣ ወግና ሥርዓት ያለው ነው። ቋንቋው ሲዳምኛ ነው። የሲዳማ ብሄር የማንነቱ መለያና መገለጫ የሆኑ የበርካታ ባህላዊ ፣ታሪካዊና ማህበራዊ የአኗኗር ዘይቤ እሴቶች ባለቤት ነው። ከእነዚህ መካከል የፊቼ ጨምበላላ በዓል ዋና እና ቀዳሚው ከሆኑ

ለድርቅ አደጋ በተጋለጡ አንዳንድ አካባቢዎች ዝናብ መዝነብ ጀምሯል

Image
በሰኔና ሐምሌ ዝናብ ባልዘነበባቸውና ለድርቅ አደጋ በተጋለጡ አፋርና ወሎ እንዲሁም ሃረርና ድሬደዋ አካባቢ ሰሞኑን ዝናብ መዝነብ እንደጀመረ ምንጮቻችን ገልፀዋል፡፡ በድርቅ አደጋ በቀን እስከ 100 የቤት እንስሳት እየሞቱ በነበረበት የአፋር ክልል በአሁን ወቅት አስቸኳይ እርዳታና ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን የጠቆሙት ምንጮቹ፤ በተለይ ከሎጊያ እስከ ክልሉ ዋና መቀመጫ ሠመራና አካባቢው ተደጋጋሚ ዝናብ እንደዘነበ ተናግረዋል፡፡ ድርቅ ተከስቶባቸው ከነበሩ ቦታዎች አንዱ የድሬደዋና ሀረር ቆላማ አካባቢ ከባለፈው ሠኞ ጀምሮ መጠነኛ ዝናብ እየዘነበ ሲሆን በድሬደዋ ከተማ ጠንከር ያለ ዝናብ መዝነቡን ለማወቅ ተችሏል፡፡ በድሬደዋ ገጠራማ አካባቢዎች ግን አሁንም የዝናቡ ሁኔታ የሚጠበቀውን ያህል አለመሆኑን ምንጮች ለአዲስ አድማስ ጠቁመዋል፡፡ ከሰሜኑ የአገሪቱ ክፍሎች አንዱ በሆነውና ከፍተኛ የድርቅ ስጋት አንዣቦበት የነበረው ከሸዋሮቢት እስከ ወሎ ባለው መስመር በሣምንቱ ተደጋጋሚ ዝናብ መዝነቡን በአካባቢው የሚገኙ ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ በምስራቅ ስምጥ ሸለቆ አካባቢ ተብሎ በሚታወቀው ከአዳማ እስከ መተሃራ ባለው አካባቢም በሳምንቱ የሚጠበቀውን ያህል ባይሆንም ዝናብ መዝነብ መቻሉን በአካባቢው የሚመላለሱ ምንጮቻችን ጠቁመዋል፡፡ የብሄራዊ ሜትሪዎሎጂ አገልግሎት ማክሰኞ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፤ በሰኔና በሐምሌ ወር በሰሜን ምስራቅ፣ በመካከለኛው እንዲሁም በመካከለኛው ምስራቅ ስምጥ ሸለቆ አካባቢዎችና በምስራቁ የሀገሪቱ ክፍሎች ከመደበኛ በታች ዝናብ መዝነቡን ጠቅሶ በነሐሴ ወር በነዚህ አካባቢዎች የዝናቡ መጠን ሊጨምር እንደሚችል ተንብይዋል፡፡ በዘንድሮ ክረምት የተፈጠረው የዝናብ እጥረት

ሂዩማን ራይትስ ዎች ለኢትዮጵያ የመረጃ ጠለፋ ቴክኖሎጂ ሸጧል ያለውን ተቋም ከሰሰ

Image
ተቋሙ ከኢትዮጵያ ጋር መስራቴን  ሙሉ ለሙሉ አቋርጫለሁ ብሏል አለማቀፉ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ሂዩማን ራይትስ ዎች ለኢትዮጵያ የመረጃ ጠለፋ ቴክኖሎጂዎችን ሸጧል፤ ለደህንነት ባለሙያዎች ስልጠና በመስጠት የዜጎች መብቶች እንዲጣሱ እገዛ አድርጓል ያለውን “ሃኪንግ ቲም” የተባለ የጣሊያን ተቋም በጉዳዩ ዙሪያ በቂ ምላሽ አልሰጠም፣ የመብቶች ጥሰቶችን ለማስቆምም እርምጃ አልወሰደም ሲል ከሰሰ፡፡ ሃኪንግ ቲም ለተለያዩ አገራት መንግስታት የመረጃ መጥለፊያ ቴክኖሎጂዎችን በመሸጥና ለባለሙያዎች ስልጠና በመስጠት፣ መንግስታት የዜጎችን ሰብአዊ መብቶች እንዲጥሱ እገዛ ያደርጋል ያለው ሂዩማን ራይትስ ዎች፣ በኢትዮጵያ ሲከናወን የቆየውን የመረጃ ጠለፋና የመብቶች ጥሰት በተመለከተ ምላሽ እንዲሰጠው ቢጠይቅም በቂ ምላሽ ሊሰጠው እንዳልቻለ ከትናንት በስቲያ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡ ተቋሙ ጉዳዩን በተመለከተ ምርመራ ለማድረግም ሆነ የኢትዮጵያ መንግስት ቴክኖሎጂውን በመጠቀም በዜጎቹ ላይ የሚያደርሰውን የመብቶች ጥሰት ለማስቆም ምንም አይነት ተጨባጭ እርምጃ አልወሰደም ሲል የከሰሰው ሂዩማን ራይትስ ዎች፣ ሃኪንግ ቲም ለኢትዮጵያ የደህንነት ባለሙያዎች የግለሰቦችን ኮምፒውተሮች ሰብረው መግባት የሚችሉበትን ስልጠና መስጠቱን እንደቀጠለና ቀጣይ ስምምነቶችን ለማድረግ እንቅስቃሴ ጀምሮ እንደነበር የሚያረጋግጡ መረጃዎችን በሃምሌ ወር እንዳገኘ አስታውቋል፡፡ ሃኪንግ ቲም ለኢትዮጵያ መንግስት የሸጣቸው የመረጃ መጥለፊያ ቴክኖሎጂዎች ከቫይረስ መከላከያ ፕሮግራሞች አቅም በላይ እንደሆኑና በቀላሉ ወደ ግለሰቦች ኮምፒውተሮች በመግባት መረጃዎችን እንደሚወስዱ የጠቆመው ሂዩማን ራይትስ ዎች፣ ከተቋሙ ኢሜይል አፈትልከው የወጡ መረጃዎችም ተቋሙ በሚያዝያ ወር ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር

Sidama

Image
  Sidamigobba, or Sidama country, extends along the Great Rift Valley from Lake Hawassa in the north to the town of Dilla in the south and from Mount Garamba in the east to the Bilaatte River in the west. The Sidama are one of the original ... Read more at: Link