«ግጭቱ ከመከሰቱ በፊት ብናመለክትም እርምጃ አልተወሰደም» - የሃዲቾ ጎሳ አባላት «አስፈላጊው እርምጃ ተወስዶ ችግሩ በቁጥጥር ስር ውሏል» - የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽንና የወንዶገነት ወረዳ አስተዳደር
ዜና ሐተታ ከደቡብ ክልል ሲዳማ ዞን ወንዶገነት ወረዳ የሃዲቾ ጎሳ አባላት አቶ ዘሪሁን ሰንበቶና አቶ ሰለሞን አለሙ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ ባስገቡት ቅሬታ « በሲዳማ ዞን የተለያዩ ቀበሌዎች ችግሩ ተፈጥሮ የአንድ ሰው ህይወት ከማለፉና ከ 60 ቤቶች በላይ ከመቃጠሉና በርካታ ንብረት ከመውደሙ በፊት ከወረዳ እስከ ክልል በየደረጃው ላሉ ተቋማትና ኃላፊዎች ችግሩ እንዳይፈጠር ብናመለክትም ሁሉም አካላት ምላሽ ባለመስጠታቸው ጉዳት ደርሷል » ብለዋል። ቅሬታ አቅራቢዎቹ የግጭቱ መንስኤ የወላቢቾ ጎሳ አባል የሆነችው ወይዘሪት መብራቴ ገልገሎ የተባለች ወጣትና የሃዲቾ ጎሳ አባል የሆነ አቶ ቢኒያም ብርሃኑ ተዋደው በመጋባታቸው የወላቢቾ ጎሳ አባላት « የሃዲቾን ጎሳ ልጅ እንዴት ያገባል። እኛ ምርጥ ዘር ነን » በሚል የጎሳው አባላት ተሰባስበው በሃዲቾ ጎሳ ላይ ጥቃት በማድረሳቸው ጉዳት መድረሱን ጠቁመዋል። የወላቢቾ ጎሳና አባላት በሃዲቾ ጎሳ አባላት ላይ ጉዳት ከማድረሳቸው በፊትና በዝግጅት ላይ እያሉ « ለወንዶገነት ወረዳ፣ ለሲዳማ ዞን አስተዳደር፣ ለደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽንና ለሚመለከታቸው ተቋማት ሁሉ ግንቦት 3 ቀን 2007 ዓ . ም አቤቱ ታችንን ብናቀርብም በወቅቱ ምላሽ ባለመስጠታቸው ጉዳቱ ተፈጥሯል » ብለዋል። በተፈጠረው ችግር የአንድ ሰው ህይወት አልፏል፣ ሌሎችም ቆስለዋል፣ ከ 60 በላይ ቤቶች መቃጠልና ዘረፋ ደርሷል፣ ቋሚ ተክሎች በገጀራ መጨፍጨፍና ሌሎች ጉዳቶችን እንዳደረሱባቸው ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅትም ለሚመለከታቸው አካላት ችግራቸውን ቢያስረዱም ከጥቃቱ ሙሉ በሙሉ መፍትሄ አለማግኘታቸውን ይናገራሉ።የፌዴራል መንግሥት ጣልቃ ገብቶ አጥፊዎችን እንዲያርምላ ቸውና በህገ መንግሥቱ የተሰጣቸውን መብት እንዲከበርላቸውም ይጠይቃሉ ። በተ