Posts

ERA Awarded Mojo – Hawassa Expressway for Keangnam

The first lot for Mojo – Hawassa Expressway project, which stretches for 93 kilometers, is awarded to a South Korean construction company, Keangnam Enterprises Limited, by Ethiopian Roads Authority (ERA). Workeneh, Gebehu, Ethiopia’s Minister for Transport, explained the firm won the bid for the first lot of the entire 209 kilometers. Even if Keangnam has won the bid the agreement between ERA and the company is not yet concluded. The project is going to be financed partially from a loan that will be secured from the South Korean Government. The difference will be covered by a state funding and the project is expected to commence in the current fiscal year. Upon completion a toll road is expected to connect the capital city of Ethiopia, Addis Ababa, with the capital of the State of Southern, Nations, Nationalities and Peoples. Samsun Wondimu, Public Relations Head at the Authority, explained Keangnam is going to handle the first phase of the project that stretches from Meki to

በሁለት ክፍለ ከተሞቿ ሲትጋይ ያደረችው ሐዋሳ እና ጥያቄ ውስጥ የገባው የከተማ ኣስተዳደር የእሳት ኣደጋን ለመቆጣጠር ያለው ዝግጅትና ብቃት

Image
ፎቶ ከ ተፈሪ ታደሰ በከተማ ታሪክ ከፍተኛ በተባለው በዚህ የእሳት ኣደጋ በሰው ህይወት እና በንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል፤ ኣላሙራ ኣዲሱ ገበያ ሙሉ በሙሉ ወድሟል፤ በተመሳሳይ ምሽት በቱላ ክፍለ ከተማም ሁለት ቤቶች በቃጠሎው ሙሉ በሙሉ መውደማቸው ታውቋል፤ የከተማዋ ኣስተዳደር መሰል የእሳት ኣደጋዎችን ለመቆጣጠር ያለው ዝግጅትና ብቃት ጥያቄ ውስጥ ገብቷል፤ በሲዳማዋ መዲና ሐዋሳ ከተማ በሁለት ክፍለ ከተሞቿ በተነሱ የእሳት ኣደጋዎች በሰው፤ በእንስሳት እና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል። የእሳት ኣደጋ የደረሰው በኣላሙራ ኣዲሱ ገበያ እና በቱላ ክፍለ ከተማ ነው። የወራንቻ ኢንፎርሜሽን ኔትዎርክ የኣይን እማኞችን ጠቅሶ እንደዘገበው፤ በታቦር ክፍለ ከተማ ፉራ ቀበሌ በሚገኘው በተለምዶ ኣዲሱ ገበያ ተብሎ በምጠራው ስፍራ ላይ ባለፈው ቅዳሜ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ላይ የተነሳው የእሳት አደጋ ገበያውን ሙሉ በሙሉ አውድሟል። ባልታወቀ ምክንያት በተከሰተውና ከሰዓታት በቆየው የእሳት ቃጠሎ አንድ የአንድ አመት ከስድስት ወር ህጻን ልጅ ህይወቱ ሲያልፍ በአንድ አዛውንት ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት መድረሱን ገልጸዋል የመንግስት ዜና ኣውታሮች የዘገቡ ቢሆንም ከተለያዩ ምንጭ የተገኙ መረጃዎች የጉዳት መጠን ከፍተኛ መሆኑን ያመለክታሉ፡፡ የእሳት ቃጠሎውን ለማጥፋት የሀዋሳ ከተማ ማዘጋጃ ቤት የእሳት አደጋ መከላከያ ብርጌድ፣ የሀዋሳ ጨርቃ ጨርቅና የሻሸመኔ ከተማ እሳት አደጋ መከላከያና የክልሉ ልዩ ሀይል ፖሊስ እሳት አደጋ መከላከያ እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪዎች የተሳተፉ ሲሆን፤ የከተማው ኣስተዳደር መሰል ኣደጋዎችን ለመቆጣጠ ያለው ዝግጁነት እና ብቃት ኣነስተኛ መሆኑ ለጉዳቱ መባባስ ምክንያት መሆኑ ታውቋል።

“ቡና ኃይለኛ የቆዳ ካንሰር ሊከላከል ይችላል”

Image
ብሔራዊ የካንሰር ኢንስቲትዩት ይፋ ያደረገው ጥናት እንደሚለው ከሆነ ቡና ሜላኖማን የመከላከል ኃይል አለው፡፡ 447 ሺህ  357  ሰዎችን ያሳተፈውና በአማካይ ለ10 ዓመታት የዘለቀው ይህ ጥናት ቡና በብዛት የሚጠጡ ሰዎች ለበሽታው ያላቸው ተጋላጭነት አነስተኛ መሆኑን አመላክቷል። በመሆኑም በቀን አራት ስኒ ቡና ወይም ከዚያ በላይ የሚጠጡ ሰዎች ለሜላኖማ የመጋለጥ ዕድላቸው ቡና ከማይጠጡ ሰዎች በ20 በመቶ ያነሰ መሆኑን ጠቁሟል። ይሁንና የጥናቱ ውጤት ያንኑ ናሙናው የተወሰደበትን ማህበረሰብ እንጂ ሌሎችን እንደማይወክልና በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ ጥናት እንደሚያስፈልግ ተመራማሪዎቹ አልሸሸጉም። ምንጭ፡-  ዘ ታይምስ ኦፍ ኢንዲያ

ድንገት የእሳት ቃጠሎ ለደረሰበት ሰው መድረግ ያለበት የመጀመሪያ ደረጃ እርዳታ

Image
•    የእሳት ቃጠሎ አደጋ የደረሰበትን ሰው በአፋጣኝ ከቃጠሎው ቦታ ማራቅ •    በጣም ያለቀዘቀዘ ወይንም በረዶ ያልሆነ ውሃን በተቃጠለው አካል ላይ ማደረግ ምክንያቱም በረዶ ቃጠሎ የደረሰበትን ቆዳችንን ስለሚጎዳ ነው። •    ማንኛውንም ልብስ ወይም ጌጣጌጥ አደጋው ከደረሰበት ሰው ላይ ማውለቅ፥ ነገር ግን ከቆዳ ጋር ተጣብቆ ያለ ማንኛውንም ነገር ለማንሳት መሞከር ለመጀመሪያ ደረጃ እርዳታ ተገቢ አይደለም፡፡ •    አደጋው የደረሰበት ሰው በብርድ እንዳይጠቃ መከላከል •    የህመም ማስታገሻ መድሀኒቶች በአቅራቢያ ካገኙ መስጠት •    በአፋጣኝ ወደ ህክምና ቦታ መውሰድ ናቸው።

በሐዋሳ ከተማ ኣዲሱ ገበያ በተከሰተው የእሳት ኣደጋ በንብረት ላይ ጉዳት ደረሰ

Image
Post by Abu Sa'adayin Fathudiin . በሐዋሳ ከተማ በተለምዶ  ኣዲሱ ገበያ ተብሎም በምታወቀው ኣከባቢ በትናንትናው እለት የተነሳው ድንገተኛ እሳት በንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱ ታውቋል። ከተለያዩ ማህበራዊ መረቦች ያገኘነው መረጃ እንደሚያመለክተው፤  አዲሱ ገበያ እና በኣከባቢው የነበሩት የንግድና መኖሪያ ቤቶች በእሳት ቃጠሎ ወድመዋል። እስከ ኣሁን ድረስ የእሳት ኣደጋው መንስዔ ምንነት ካለመታወቁ በላይ በንብረት ላይ የደረሰው ጉዳት በገንዘብ ስተመን ምን ያህል ልሆን እንደምችልም የተነገረ  ነገር የለም።