Posts

Dozens of migrants drown in shipwreck off Red Sea

Dozens of migrants drown in shipwreck off Red Sea

የውጭ ቦንድ ሽያጩና ሥጋቶቹ

Image
እ.ኤ.አ. በ2012 መጨረሻ አቅራቢያ፣ ሊበርታድ የተባለችውና ንብረትነቷ የአርጀንቲና ባሕር ኃይል የሆነችው ወታደራዊ ማሠልጠኛ መርከብ በዓለም አቀፍ የሕግ አስከባሪ አካል በቁጥጥር ሥር የዋለችው፣ በጋና ቴማ ወደብ አቅራቢያ ሲሆን በዚያ ለሁለት ወራት ከሁለት ሳምንት እንድትቆይ ተገዳለች፡፡ ከዚህች መርከብ ባሻገር ንብርትነቱ የአርጀንቲና የሆነው ፕሬዚዳንታዊ አውሮፕላንም ሲበር ከነበረበት አገር ተይዞ በቁጥጥር ሥር ለመዋል በቅቷል፡፡ በዚህ አላበቃም፡፡ በአሜሪካው ፌዴራል ሪዘርቮ ባንክ የሚከማቸው የአርንቲና ማዕከላዊ ባንክ ተቀማጭ እንዳይንቀሳቀስ ከመደረጉ በላይ እንዲወረስ መደረጉ የሚታወስ የቅርብ ጊዜ ክስተት ነው፡፡    አርጀንቲናውያን ከጥቂት ሰዎች በተበደሩት ገንዘብ ሳቢያ ዕዳ አለባቸው እንበል፡፡ እውነታው ይሄው ነው፡፡ መሠረቱ በአሜሪካ ሆነ መቀመጫውን ኬመን ደሴት ያደረገውና ከአሜሪካ ውጭ በመንቀሳቀስ፣ የተለያዩ ፈንዶችን በማስተዳደር ከሚታወቀው ኤንኤምኤል ካፒታል ከተባለው ኮርፖሬሽን ጋር በተፈጠረ ቅራኔ ሳቢያ ነበር ንብረቶቹ የታገዱት፡፡ የኒውዮርክ ፍርድ ቤት በፍትሐብሔር ክስን ባስቻለበት ወቅት፣ ኤንኤምኤል ኮርፖሬሽን በአርጀንቲና ያለኝ ከ800 ሚሊዮን ዶላር በላይ ዕዳ ይከፈለኝ ሲል ጠይቋል፡፡    አርጀንቲና እ.ኤ.አ በ2001 በነበረባት የ82 ቢሊዮን ዶላር የብድር ቃልኪዳን ሰንድ (ሶቨሪን ቦንድ) ዕዳ በወቅቱ ለመክፈል አልቻለችም ነበር፡፡ እ.ኤ.አ. ከ1989 እስከ 2000 ድረስ በዘለቀውና አርጀንቲናን በመታው የፋይናንስ ቀውስ ሳቢያ፣ አገሪቱ ያለባትን የብድር ዕዳ ለመክፈል ሳትችል መቅረቷ፣ የአገሪቱን የቦንድ ሰርቲፊኬት የገዙ የውጭ ኢንቨስተሮችን ድንጋጤ ውስጥ የከተተ ክስተት ነበር፡፡ አርጀንቲና ዕዳዋን ለመክፈል አለመቻሏ ብቸኛ አገ

ጡማኖ እና ፋቂሳ

Image
ቴላሞ የጡማኖ  መታሰቢያ sidma tomano memoraial የጡማኖ መካነ መቃብር እና የሃገር ሽማግሌው አቶ ሲዳሞ ቢረጋ ከለኩ ከተማ በስምንት ኪሎ ሜትር ገደማ ርቀት ላይ የሚገኘው ቴላሞ ነው፤ ቴላሞ የሲዳማ አድባር ነው ሲሉ የሃገር ሽማግሌዎቹ ይገልጻሉ፡፡ አረንጓዴ ምድር ምን ማለት እንደሆነ በቴላሞ ቅጥር ግቢ ያሉት ሃገር በቀል ግዙፍ የዛፍ ዝርያዎች ለትውልድ የቆሙ ማስረጃዎች ናቸው፡፡ መልከአ-ምድራዊ ውበቱ ይማርካል፤ ከደኑ መሃል በአጥር የተከበበ አንድ ቅጥር አለ፤ በዚህ ቅጥር ውስጥ የሲዳማ ነገድ አባት የሆነው የጡማኖ መቃብር ይገኛል፡፡ በስፍራው በየእጽዋቱ ስር የአረብኛ ጽሁፍ ያለባቸው ድንጋዮች ይገኛሉ፤ እንደ አካባቢው ሽማግሌዎች ገለጻ እነዚህ የአረብኛ ጽሁፍ ያለባቸው ድንጋዮች መቃብሮች ናቸው፡፡ ሲዳሞ ቢራጋ የሃገር ሽማግሌ ናቸው፤ በየግዜው ለተለያየ ጉዳይ ወደ ቴላሞ ይመጣሉ፤ ይህንን ስናጠናቅር በስፍራው ያገኘናቸውም ለተመሳሳይ ዓላማ በቴላሞ ውብ ቅጥር ግቢ ለውይይት አረፍ እንዳሉ ነው፡፡ የሲዳማ የሃገር ሽማግሌዎች የሚለብሱትን ባህላዊ አለባበስ የለበሱት አቶ ሲዳሞ ቢራጋ ስፍራውን በሚመለከት አንዳንድ ጥያቄዎችን ስናቀርብላቸው በማራኪ አተራረክ ለዛ መልሰውልናል…መነሻችን ደግሞ ቴላሞ ምንድን ነው የሚል ነበር አቶ ሲዳሞ በተረጋጋ ሁኔታ ረጃጅም የቅጥሩ ዛፎች ላይ አይናቸውን ተክለው አብራሩልን….   ይሄ ቦታ ቴላሞ ይባላል፤ ጡማኖ የሲዳማ አባት ነው፤ እዚህ ነው የተቀበረው፤ ቦታው ብዙ ዓመቱ ነው….ማን ይቆጥረዋል ብዙ ነው፤ እዚህ የወለደ ሰው አሁን አስራ ስድስት ትውልድ ሆኗል፡፡ የቅጥሩን ዙሪያ ገባ በዓይናቸው ቃኘት አድርገው መልሰው ወደ ሽማግሌዎቹ በመመልከት የቴላሞን አካባቢ ሁለንተናዊ እሴት በወፍ በረር መተረኩን ቀጥለዋ

በብራዚል የተከሰተውን ድርቅ ተከትሎ ኢትዮጵያ የቡና ገበያውን ለመምራት መዘጋጀቷ እየተነገረ ነው፤ ለመሆኑ የቡና ኣብቃይ ኣርሶ ኣደሮች ተጠቃሚነትን ለማሳደግ ምን ታስቧል?

Image
በዓለም ላይ ከፍተኛውን ቡና በምታቀርበው ብራዚል የተከሰተውን ድርቅ ተከትሎ ኢትዮጵያ የቡና ገበያውን ለመምራት መዘጋጀቷ እየተነገረ ነው። ለዚሁም የኣገሪቱ መንግስት እና ቡና ላኪዎች ከኣጋጣሚው ተጠቃሚ ለመሆኑ በመስራት ላይ መሆናቸው ታውቋል። ለመሆኑ የቡና ኣብቃይ ኣርሶ ኣደሮች ተጠቃሚነትን ለማሳደግ ምን ታስቧል?  የኣገሪቷን የቡና ኣቅርቦት ለማሳደግ በመሰራት ላይ መሆኑን በተመለከተ የቀረበ ዘጋባ፦ በዓለም ላይ ከፍተኛውን ቡና በምታቀርበው ብራዚል የተከሰተውን ድርቅ ተከትሎ ኢትዮጵያ የቡና ገበያውን ለመምራት እንደተዘጋጀች የኢትዮጵያ ቡና ላኪዎች ማህበር ገለጸ። የማህበሩ ሊቀመንበር አቶ ሁሴን አግራው እንደሚሉት በጎርጎሮሳውያኑ 2014/15 መጨረሻ ከ235 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለውጭ ገበያ በማቅርብ 8 መቶ 62 ሚሊየን ዶላር ገቢ ለማግኘት እየተሰራ ነው። በብራዚል የተፈጠረውን የቡና ምርት መቀነስ ምክንያት በማድርግ ኢትዮጵያ በሰፊው ለዓለም ገበያ ቡናን ለማቅረብ እንደምትሰራ ገልጸዋል። ከለፈው ሐምሌ  ጀምሮ ባሉት አራት ወራት ኢትዮጵያ 54 ሺህ ቶን ቡናን ለዓለም ገበያ በማቅረብ ከአፍሪካ ቀዳሚዋ ሆናለች። ከዚህም 2 መቶ 32 ሚሊየን ዶላር  ገቢ ማግኘት ችላለች፡፡ ይህ አሃዝ ከባለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከ59 ሚሊየን ዶላር በላይ ብልጫ አለው። ምንጭ፦ ኢብኮ

በሃዋሳ ከተማ ኣሽናፊነት የተጠናቀቀው 6ኛው የከተሞች ፎረም

Image