Posts

የፀረ ሙስና ኮሚሽን በቡና ወጪ ንግድ ችግሮች ላይ ያካሄደው ጥናት መጠናቀቁ ተሰማ

የፌዴራል ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በቡና የወጪ ንግድ ላይ በተፈጠሩ ችግሮች ዙሪያ ሲያካሂድ የቆየውን ጥናት ማጠናቀቁን ምንጮች ገለጹ፡፡ ኮሚሽኑ ሕገወጥ ሥራ ሠርተዋል ባላቸው ላይ ዕርምጃ ለመውሰድ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ጋር እየተነጋገረ መሆኑ ታውቋል፡፡ የፀረ ሙስና ኮሚሽን ረዘም ያለ ጊዜ ወስዶ ሲያካሂድ የቆየው ምርመራዊ ጥናት ተጠያቂ የሚሆኑትን እንደለየ የሚናገሩት ምንጮች፣ በቀጣይነት መወሰድ ባለበት ሕጋዊ ወይም አስተዳደራዊ ዕርምጃ ላይ በከፍተኛ ባለሥልጣናት ደረጃ ውይይት እየተካሄደ መሆኑን ይናገራሉ፡፡ ነገር ግን የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ወዶ አጦ፣ ጥናቱ እየተካሄደ መሆኑን ነገር ግን ገና አለመጠናቀቁን ተናግረዋል፡፡ የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ምንጮች ግን ኮሚሽኑ በንግድ ሚኒስቴርና በቡና ላኪዎች ላይ ትኩረት አድርጎ ሲያካሂድ የቆየውን ጥናት ማጠናቀቁን ተናግረዋል፡፡ ጥናቱ ትኩረት ካደረገባቸው ጉዳዮች መካከል ንግድ ሚኒስቴር በቡና ላኪዎች ላይ በቂ ክትትልና ቁጥጥር አለማድረጉ፣ የተሟላ የመረጃ አያያዝ ሥርዓት አለመኖሩ፣ በሁሉም ድርጅቶች ላይ ወቅቱን የጠበቀ የቡና ክምችት ቆጠራ አለመካሄዱ፣ ለውጭ ገበያ የተዘጋጀን ቡና ኤክስፖርት በማያደርጉ  ነጋዴዎች ላይ ዕርምጃ አለመወሰዱ፣ በኢትዮጵያ ምርት ገበያ በሚሸጥ የቡና ገለፈት ላይ ተገቢውን ቁጥጥርና ክትትል አለመደረጉ ተጠቃሾች ናቸው፡፡ ከዚህ በላይ ጐልቶ የታየው ችግር ደግሞ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ፈቃድ ሳይሰጥ ቡናን ወደ ውጭ አገር ኤክስፖርት ማድረግ ነው፡፡ ብሔራዊ ባንክ ወደ ውጭ ለሚላክ ቡና የሚሰጠው ፈቃድ አለ፡፡ ይህ ፈቃድ ካልተገኘም ቡና ወደ ውጭ መላክ የተከለከለ ነው፡፡ ነገር ግን የተወሰኑ ነጋዴዎች ይህ ፈቃድ ሳይኖራቸው

ሃዋሳ

Image
http://www.diretube.com/walta/a-closer-look-hawassa-city-video_29dadc2b7.html

ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ አለም አቀፍ የቦንድ ሸያጭ ገበያን ዛሬ ትቀላቀላለች

Image
( ኤፍ.ቢ.ሲ ) ኢትዮጵያ ዛሬ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ አለም አቀፍ የቦንድ ሸያጭ ገበያን ትቀላቀላለች ተብሎ እየተጠበቀ ነው። ለሽያጭ ይቀርባል ተብሎ የሚጠበቀው የቦንድ መጠንም 1 ቢሊየን ዶላር መሆኑ ተነግሯል። አገሪቱ ከቦንድ ሽያጩ አስቀድሞ በአገሪቱ ውስጥ ስላሉ ምቹ የኢንቨስትመንት ሁኔታዎችና በምትሸጠው ቦንድ የምታገኘውን ገንዘብም ለምን ለምን ተግባራት ልታውለው እንዳሰበች በአውሮፓና በአሜሪካ ለሚገኙ የገንዘብ አበዳሪ ባለሀብቶች ለአንድ ሳምንት የዘለቀ ገለፃ ስታደርግ ቆይታለች። ይህን ገለፃዋንም ትናንት ለመጨረሻ ጊዜ በአሜሪካ ኒውዮርክ ከተማ ለሚገኙ ባለሀብቶች በማቅረብ ማጠናቀቋንም ፋይናንሽያል ታይምስ ዘግቧል። በኒውዮርክ ገለፃ ላይ የተገኙት ባለሀብቶችም በአጠቃላይ ኢትዮጵያ እየተጓዘችባቸው ስላሉት ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ነባራዊ ሁኔታዎች ተብራርቶላቸዋል። እንደዘገባው ከሆነ በዛሬው ዕለት ጄ ፒ ሞርጋንና ደች ባንክ የኢትዮጵያን ቦንድ ለአለም አቀፍ አበዳሪ ባለሀብቶች ይዘው እንደሚቀርቡ ይጠበቃል። ኢትዮጵያ የተበደረችውን ገንዘብም በ10 ዓመታት ውስጥ የምትመልስ ይሆናል። የአለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም አይ ኤም ኤፍ በዚህ ዓመት ኢኮኖሚያቸው በፍጥነት ይመነደጋል ብል ካስቀመጣቸው አገራት መካከል ኢትዮጵያን በስምንተኛነት አስቀምጧታል። የኢትዮጵያ መንግስት ኢኮኖሚያዊ ዕድገቱን ለማስቀጠል ያለው ቁርጠኝነትም ቦንዱን ለሚገዙ የገንዘብ አበዳሪ ባለሀብቶች አስተማማኝ እፎይታን እንደሚያጎናፅፋቸው ተገምቷል።

Ethiopia's Zone9 Bloggers Face the Limits of International Law

Image
The international human rights system is broken – or perhaps it never worked at all. In case after case, citizens’ human rights are violated under the national laws of their respective countries, despite the existence of international human rights commitments in the United Nations’ Universal Declaration, and by the Organization for Security and Cooperation in Europe, the Organization of American States, the African Commission, and others. The International Criminal Court has little say concerning any but the most egregious of international human rights violations, and member states have wide latitude to dispense justice as they see fit. For those who live in countries that fail to provide or enforce their own laws protecting freedom of expression, international principles have rarely provided actual recourse. Today, this is the case with the independent Ethiopian blogger collective known as Zone9. In April of this year, the government of Ethiopia arrested six members of Zone9

Ethiopia sees record coffee exports after Brazil's drought

( Reuters ) - Ethiopia expects coffee exports for its 2014/15 crop to hit a record high because of drought and disease stifling crops in Latin America, the head of its exporters association said on Wednesday. An unprecedented drought early this year reduced the 2014/15 crop in the world's biggest coffee producer Brazil. The International Coffee Organization forecast in September that global coffee production will fall short of demand. In the four months from July this year, Ethiopia - Africa's biggest producer of the bean - exported 54,000 tonnes of coffee worth $231.9 million, compared with the $172.5 million it earned from 51,000 tonnes over the same period last year. Hussein Agraw, chairperson of the Ethiopian Coffee Exporters' Association, said he expected the amount of coffee exported to rise to 235,000 tonnes by the end of 2014/2015, generating $862 million in revenue. Ethiopia exported around 190,000 tonnes in 2013/14, earning $841 million, he said. Exports