ሙስናን በክልሎች ለመከላከል መንግሥት የፖለቲካ ውሳኔ መስጠት አለበት ተባለ
‹‹በፌዴራል ሥርዓት ውስጥ ጣልቃ መግባት ሕገ መንግሥቱን መጣስ ነው›› አቶ አስመላሽ ወልደ ሥላሴ በክልሎች፣ ብልሹ አሠራርና ሙስናን ለመከላከል፣ የክልል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽኖች በአመራሮች ተፅዕኖ በአግባቡ መሥራት ባለመቻላቸው የፌዴራል መንግሥት ፖለቲካዊ ውሳኔ እንደሚያስፈልግ የፌዴራል የሥነ ምግባር የፀረ ሙስና ኮሚሽን አሳሰበ፡፡ ኮሚሽኑ የአገር አቀፍ የፀረ ሙስና ጥምረት ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አሥረኛ መደበኛ ስብሰባውን ኅዳር 11 ቀን 2007 ዓ.ም. በሸራተን አዲስ ለግማሽ ቀን ባካሄደት ወቅት እንደገለጸው፣ በየክልሉ ያሉ የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ተቋማት በነፃነት እንዳይሠሩ የክልሎቹ አመራሮች ተፅዕኖ እያደረሱባቸው መሆኑን አስታውቋል፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የሕግና አስተዳደር ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ በአቶ አስመላሽ ወልደሥላሴ ሰብሳቢነት በተካሄደው አሥረኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ የተወሰኑ ባለድርሻ አካላት ብቻ ተገኝተዋል፡፡ የአገር አቀፍ የፀረ ሙስና ጥምረትና የፌዴራልና የክልል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽኖች የ2006 በጀት ዓመት ሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ካቀረቡ በኋላ፣ በተገኙት ጥቂት ባለድርሻ አካላት የተለያዩ ጥያቄዎች ተነስተዋል፡፡ በተለይ በአፋር፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝና በሶማሌ ክልሎች የፀረ ሙስና ተቋማት በነፃነት እየሠሩ እንዳልሆነና ያላቸውን ከፍተኛ ሀብት እንደ አገር መጠቀም አለመቻሉን ተሳታፊዎቹ ተናግረዋል፡፡ በክልል የሚገኙ አመራሮች እነሱ እንዲከሰስ የፈለጉትን የኮሚሽኑ ኃላፊዎች ካልከሰሱ ወይም መከሰስ የሌለባቸውን ከሰው ከተገኙ፣ ከኃላፊነታቸው እንደሚያነሷቸውና በፈለጉት ቦታ እንደሚመድቧቸው ጠቁመዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ የአፋር ክልል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙና ኮሚሽን ኃላፊ እንደሌለው የጠቆሙት የስብ