Posts

ሲዳማ ቡና የሊጉን መሪነት ከደደቢት ተረከበ

Image
ትናንትና በተደረጉ 4 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች አዳማ ከነማ እና ሲዳማ ቡና ድል አድርገዋል፡፡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ደግሞ በአስገራሚ መልኩ አቻ ተለያይቷል፡፡ በአዲስ አበባ ስታድየም 9፡00 ላይ መከላከያ አርባምንጭ ከነማን አስተናግዶ 0-0 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይቷል፡፡ ጨዋታው ተመጣጣኝ የነበረ ሲሆን አልፎ አልፎ ከተደረጉ ሙከራዎች ውጪ ይህ ነው የሚባል እንቅስቃሴ ሳይታይበት ተጠናቋል፡፡ ቀጥሎ በአዲስ አበባ ስታድየም የተካሄደው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ሙገር ሲሚንቶ ጨዋታ በግቦች እና ሙከራዎች እንዲሁም በፈጣን እንቅስቃሴዎች የታጀበ ጨዋታ ነበር፡፡ ንግድ ባንኮች በመጀመርያዎቹ 5 ደቂቃዎች 3 ያለቀላቸው የግብ እድሎችን ያመከኑ ሲሆን ፊሊፕ ዳውዚ በ17ኛው ደቂቃ በፊሊፕ ዳውዚ ፣ በ37 ኛው ደቂቃ በአዲሱ ካሳ በተቆጠሩ ግቦች 2-0 መርተው የመጀመርየውን አጋማሽ አጠናቀዋል፡፡ በሁለተኛው አጋማሽ ሙገር ሲሚንቶዎች ግርማ ኃ/ዮሃንስ በወሰዱት የተጫዋች ቅያሪ እርምጃ ታግዘው ባልተጠበቀ ሁኔታ አከታትለው ባስቆጠሯቸው ግቦች ወሳኝ አንድ ነጥብ ይዘው ተመልሰዋል፡፡ ለሙገር ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ያሳረፈው ተቀይሮ የገባው ጋናዊው አጥቂ ጌድዮን አካፖ ነው፡፡ አዳማ ላይ ዘንድሮ ፕሪሚየር ሊጉን የተቀላቀሉት አዳማ ከነማ እና ወልድያ ተገናኝተው አዳማ ከነማ በቀላሉ 3-1 አሸንፎ የውድድር ዘመኑን የመጀመርያ 3 ነጥብ አሳክቷል፡፡ ይርጋለም ላይ በሜዳው ጠንካራ የሆነው ሲዳማ ቡና 1-0 ከመመራት ተነስተው በመጨረሻዎቹ 15 ደቂቃዎች ባስቆጠሩት ግብ ዳሽን ቢራን 2-1 አሸንፈው የሊጉ መሪነትን ከደደቢት የተረከቡበትን ድል አስመዝግበዋል፡፡ ቀሪዎቹ 3 የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች በብሄራዊ ቡድኑ ዝግጅት ምክንያት ላልተወሰነ ጊዜ የተራዘሙ ሲሆን ፕሪ

ሴት ተማሪዎችን የማብቂያ መንገዶች... እና በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሲዳማ ቋንቋ የሶስተኛ ዓመት ተማሪ ንጋቷ ዮሐንስ ኣስተያየት

Image
አዲስ የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ሆኖ፣ አካባቢ ቀይሮ፣ ከቤተሰብ ርቆ መሄድ ትልቅ ፈተና ነው። በተለይ ደግሞ ሴትነት ሲጨመርበት ፈተናው እጥፍ ድርብ ይሆናል። የዩኒቨርሲቲ ህይወት ከቤተሰብ ቁጥጥር ውጪ የሚኮንበት፣ ራስን በራስ ማስተዳደር የሚጀመርበት ወቅት በመሆኑ፣ በዚያ ላይ ወጣትነት ተዳምር ሁኔታዎቹ ሁሉ ለጥፋት የተመቻቹ ይሆናሉ። እናም አንዳንድ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከዓላማቸው ውጪ ሆነው ሲሰናከሉ ይታያሉ - በተለይ ሴቶች። ተማሪ ንጋቷ ዮሐንስ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሲዳማ ቋንቋ የሶስተኛ ዓመት ተማሪ ናት። ሴት ተማሪዎች የሚሰናከሉበትን ዘመን እሷ ጠንክራ ተወጥታዋለች። ወደ ዩኒቨርሲቲው ከተቀላቀለችበት ካለፈው ሶስት ዓመት ጀምሮ በዩኒቨርሲቲው ብዙ ለውጦችን ማየቷን ትናገራለች። በአካዳሚም ሆነ በግቢው ውበት ዩኒቨርሲቲው እጅግ ብዙ ለውጥ አሳይቷል። በተለይ ደግሞ ሴት ተማሪዎችን ለማብቃት የሚሰራው ስራ አበረታች ነው ስትል ትገልፀዋለች። ተማሪ ንጋቷ ተወልዳ ያደገችው በሲዳማ ዞን ሸበዲኖ ወረዳ ውስጥ ነው። ከአንደኛ እስከ 12 ኛ ክፍል የተማረችውም በተወለደችበት አካባቢ ሲሆን፤ ከቤተሰብ ተለይታ ወደ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የመጣችው ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ያኔ የተለያዩ ስጋቶች ነበሯት። ሆኖም ግን በዩኒቨርሲቲው ያገኘችው የተለያየ ድጋፍ በትምህርቷ በጥሩ ነጥብ እንድትቀጥል አስችሏታል። « ዩኒቨርሲቲው ለሴት ተማሪዎች የተለያየ ድጋፍ ነው የሚያደርገው። በተለይ የኢኮኖሚ አቅማቸው አነስተኛ ለሆኑ ሴቶች የገንዘብ ድጋፍ ያደርጋል። ለሴት ተማሪዎች ብቻ መገልገያ በባለሙያ የተሟላ ክሊኒክ፣ ማደሪያ ቤታችን አካባቢ ደግሞ ቤተመጻሕፍት ተከፍቷል። እንዲሁም በተለያዩ መምህራን የማጠናከሪያ ትምህርት ይሰጣል » በማለት በዩኒቨርሲቲው የሚደረገውን ድጋፍ

ተመድ ዜግነት የሌላቸው ወገኖች መፍትሄ እንዲያገኙ ጥረት ላይ ነኝ አለ

Image
በአለም ላይ ዜግነት አልባ የሆኑ ወገኖችን በ10 ዓመታት ውስጥ መፍትሄ እንዲያገኙ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን  አስታወቀ፡፡ እንደ ኮሚሽኑ መረጃ በአሁኑ ወቅት በአለም ላይ ቢያንስ 10 ሚሊዮን የሚሆኑ ፓስፖርትም ሆነ ዜግነት ሳይኖራቸው በጥገኝነት የሚኖሩ ሰዎች አሉ፡፡ በየ10 ሰከንዶቹም ዜግነት የሌላቸው ህፃናት ይህችን አለም ይቀላቀላሉ፡፡ በዚህም ምክንያት እነዚህ ስደተኞች የጤናና የትምህርት እንዲሁም እንደ መምረጥ ያሉ ፖለቲካዊ መብታቸውን ተነፍገው ይኖራሉ፡፡ የተመድ የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን ታድያ ሀገራት ዜግነት የሌላቸውን ህፃናትና የማህበረሰብ ክፍሎች ዜግነት እንዲያገኙ ለማረግ  እንደሚንቀሳቀስ ነው ያስታወቀው፡፡      በየተለያየ ምክንያት ሰዎች ዜግነት ላይኖራቸው አልያም ዜግነታቸውን ሊያጡ ይችላሉ፡፡ በተለይም በስደተኛ መጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ የሚወለዱ ህፃናት የተወለዱበት ሀገር ዜግነትም ሆነ የወላጆቻቸውን ዜግነት የማግኘት እድላቸው ጠባብ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ችግሩን እንደሚጎላ መረጃዎች የመለክታሉ፡፡ እንደ የማይናማሮቹ የሮሂጋ አናሳ ጎሳዎች የማንነት ጥያቄያቸው አሁንም መልስ አለማግኘትና የዜግነት መብቶቻቸውንም ተነፍገው የሚኖሩ ናቸው፡፡ በ27 ሀገራት እናቶች ለልጆቻቸው ዜግነታቸውን ማስተላለፍ የማይችሉ ሲሆን እንደ የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን እነዚህ ምክንያቶች ዜግነት አልባ ትውልድ እየፈጠረ ይገኛል፡፡ ዜግነት አልባነትን ከአለም ላይ ጨርሶ ለማሶገድ እንደጎርጎሮሳዊያኑ አቆጣጠር  የ1954ቱን የዜግነት አልባ ሰዎች ሁኔታ ስምምነትና የ1961ዱን የዜግነት አልባነት ቅነሳ ስምምነቶች ተግባራዊነት ላይ ትኩረት አድርጎ እንደሚሰራኮሚሽኑ አስታውቋል፡፡   ምንጭ፡- EBC

LibreOffice Linux - Deb (x86_64) version 4.3.3, Sidamas is available to download

Image
Source: http://et.libreoffice.org/allalaadimine/?type=deb-x86_64&lang=sid&version=4.3.3

የዝቅተኛ ደመወዝ ወሰንየለሹ ኢኮኖሚ

Image
ያሰረችው የወየበ ሻሽ ሙሉ በሙሉ ፀጉሯን አልሸፈነላትም፡፡ አቧራ የጠጣው ፀጉሯ በዚህም በዚያም አፈትልኮ ይታያል፡፡ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 17 አቅራቢያ ከሚገኝ የግንባታ ሳይት ላይ ያገኘናት አብነት ነጋሽ፣ ፀሐይ የጠበሰው ፊቷ ስለ ሥራዋ ፈታኝነት ብዙ ይናገራል፡፡ ምንም እንኳ ወቅቱ ሙቀት ቢሆንም አብነት በልብስ ላይ ልብስ ደራርባለች፡፡ ሱሪ፣ በሱሪ ላይ ቀሚስ፣ ሹራብ፣ አንገቷ ላይ ሻርፕ አድርጋለች፡፡ በካልሲ የተጫማችው አሮጌ ኮንጐ እንደዚያ መውጣት መውረድ ባለበትና ከፍተኛ ጥንቃቄ በሚጠይቅ የሥራ አካባቢ ምቾት የሚሰጥ አይመስልም፡፡ ምንም እንኳ ከታች እስከ ላይ እንደዚያ መልበሷ ከሥራው ጋር እንዲሄድ በማሰብ ቢሆንም፡፡  ሸዋ ምንጃር አካባቢ የተወለደችው የ33 ዓመቷ አብነት የምትኖረው ገርጂ አካባቢ ሲሆን ከሥራ ቦታዋ የምትገኘው ማልዳ በመነሳት በእግሯ ተጉዛ ነው፡፡ መንገዱ አንድ ሰዓት የሚወስድባት ሲሆን ዘወትር ጠዋት አንድ ሰዓት ላይ ከሥራ ገበታዋ ትገኛለች፡፡ ትራንስፖርት፣ ቁርስና አለባበስ የሚባሉ ነገሮች ለሷ ብዙ ትርጉም የሚሰጡ ነገሮች አይደሉም፡፡ ስትመለስም በተመሳሳይ መልኩ በእግሯ እያዘገመች ነው፡፡ ረዥም ሰዓት መሥራት፣ በቀላሉ ንፁህ ውኃ ማግኘት አለመቻል፣ በተወሰነ መልኩ እንኳ ተመቻችተው ልብስ የሚቀይሩበት ወይም የሚመገቡበት ቦታ አለመኖር የየዕለቱ የሥራ ላይ ፈተናዎቿ ናቸው፡፡ በቀን የሚከፈላት 35 ብር ነው፡፡ ‹‹ቀን በቀን ሁሉም ነገር እየጨመረ የሚከፈለው ምንም ማለት አይደለም፡፡ ግን ደግሞ ካልሠራን ምን እንበላለን፤›› ትላለች፡፡  ወርቅነህ ፈለቀ የመንገድ ሥራ ላይ በተሰማራ አንድ ኮንስትራክሽን ኩባንያ የፌራዮ ሠራተኛ ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል፡፡ ምንም እንኳ ድርጅቱ በመንገድ ሥራው ላይ ከተሰማራ ከሞላ ጐደል ሁለት