ሐዋሳን እንዳየኋት
ሐዋሳን እንዳየኋት በአገራችን ውስጥ በከፍተኛ ደረጃ በማደግ ላይ ካሉ ከተሞች ውስጥ አንዷ ሐዋሳ ናት፡፡ የኢንዱስትሪ ዞን ከተማ ከሆኑትም አንዷ ናት፡፡ የውጭ አገርና የአገር ውስጥ ጎብኝዎች በስፋት የሚስተናገዱባት በሆነችነችው ሐዋሳ ከተማን በጎበኘሁ ጊዜ የሚከተሉትን ችግሮች መመልከት ችያለሁ፡ ይኸውም እንዲሰጣቸው የሚፈልጉትን የገንዘብ መጠን ወስነው ካልሰጣችሁኝ የሚሉ ለማኞች እንዲሁም የቆሙ መኪናዎች ዕቃ ሥርቆት እየተስተዋለ ይገኛል፡፡ ይህ ድርጊት በጊዜ ቁጥጥር ሥር ካልዋለ፣ ለከተማዋ ዕድገትና መሻሻል እንዲሁም የተሻለ ገቢ ለማግኘት መሰናክል ስለሚሆን የተከማው አስተዳደር እነዚህን ችግሮች ትኩረት ሰጥቶ ፈጣን መፍትሔ መስጠት ወይም ዕርምጃ መውሰድ ይገባዋል እላለሁ፡፡ (አማን ኑሪ፣ ከአዲስ አበባ) ቤቶች ኤጀንሲ ለሹማምንት ቤት የሚሰጠው ከማን ወስዶ ነው? ‹‹የመንግሥት ቤቶች ኤጀንሲ ለተሿሚዎች ቤት እንዲያቀርብ ታዘዘ፤ የሚያቀርበው ቤት ባለመኖሩ ደንበኞች ላይ ትኩረት ተደርጓል፡፡›› በማለት የሪፖርተር የእሑድ መስከረም 25 ቀን 2007 ዓ.ም. ዕትም፣ የውስጥ ዜና አስነብቧል፡፡ ይህንን ዜና ተንተርሼ ከፍትሕ አካላት ራሱን ነጥሎ ኢፍትሐዊ የሆነ ዕርምጃን በመውሰድ የሚታወቅን ተቋም ይባስ ብሎ ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ በራሱ አስፈጻሚዎች ነዋሪውን ከቤቱ እንዲያስወጣ ሥልጣን ስለተሰጠው የመንግሥት ቤቶች ኤጀንሲ የማውቃቸውን እውነታዎችና እንደዚህ ዓይነቶቹ ኢፍትሐዊ አካሄዶች በዜጎችና በመንግሥት ላይ የሚያሳድሩት ጥሩ ያልሆኑ ተፅዕኖዎችን ለማሳየት ግድ ብሎኛል፡፡ የመንግሥት ቤቶች ኤጀንሲ ከከተማ ትርፍ መሬትና ቤት አዋጅ ጋር በተገናኘ የተወረሱ ቤቶችን ማለትም ኪራያቸው ከመቶ ብር በላይ የሆኑትን ቤቶች እንዲቆጣጠርና የቤት አቅር