Posts

SIDAMA BEAUTY

Image
Photo:  Dodho Magazine  

በፈረንጆቹ 2015 አንድ ሚሊየን የኢቦላ መከላከያ ክትባት ይሰራጫል- የአለም የጤና ድርጅት

Image
አንድ ሚሊየን የኢቦላ መከላከያ ክትባት በፈረንጆቹ 2015 ለማሰራጨት መዘጋጀቱን የአለም የጤና ድርጅት አስታወቀ። በቀጣይ አመት አጋማሽ ብቻ በብዙ መቶ ሺህ የሚቆጠሩ ክትባቶች በቫይረሱ ክፉኛ በተጠቁት ጊኒ፣ ላይቤሪያ እና ሴራሊዮን በተያዘው ዓመት ነሃሴ ወር ላይ እንደሚሰራጩም ነው የገለፀው። ይሁንና ክትባቱ የኢቦላን ስርጭትን ለመግታት ከሚደረገው ህሉን አቀፍ ጥረት በላይ ተዓምር መፍጠር የሚችል መሳሪያ ተደርጎ እንዳይወሰድም አሳስቧል። የኢቦላ ቫይረስ እስካሁን የ4 ሺህ 500 ሰዎችን ህይወት ቀጥፏል። በኢቦላ ቫይረስ ተይዞ ካገገመ በሽተኛ የተወሰደን ደም በመጠቀም የኢቦላ ቫይረስን ለመከላከል የሚያስችል ክትባት ለመስራት መዘጋጀቱንና በፈረንጆቹ 2015 ተግባራዊ እንደሚደረግ የአለም የጤና ድርጅት ምክትል ዳይሬክተር ዶክተር ፓውል ኬኒ ቀደም ብለው መናገራቸው ይታወሳል። ምንጭ፦  ኤፍ.ቢ.ሲ

Moon, Kim to Visit Ethiopia

Image
Two most notable international personalities are due to visit Ethiopia next week, sources disclosed to  Fortune . Ban Ki Moon, secretary general of the United Nations, and Jim Yong Kim (PhD), president of the World Bank, are scheduled to arrive here in Addis Abeba on October 27, 2014, to visit projects financed by the two organizations. This will not be Moon’s first visit to Ethiopia, although it will be for Kim, the duo will stay here for two days, these sources disclosed.

ዋሊያዎቹ በወዳጅነት ጨዋታ ኡጋንዳን ሊገጥሙ ነው

Image
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የኡጋንዳ አቻውን በወዳጅነት ጨዋታ ሊገጥም ነው። የኡጋንዳ ብሄራዊ ቡድን በ2015ቱ የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ለማለፍ ከጋና ጋር ለሚያደርገው ጨዋታ እንዲጠቅመው ነው ከዋሊያዎቹ ጋር የአቋም መፈተሻ ጨዋታ የሚያደርገው። “ዘ ክሬንስ” የፊታችን ጥቅምት 30 በማንዴላ ብሄራዊ ስታዲየም ዋሊያዎቹን ያስተናግዳሉ። የሀገሪቱ እግር ኳስ ፌደሬሽን የበላይ ጠባቂ ኢድጋር ዋትሰን እንደተናገሩት፥ የወዳጅነት ግጥሚያው ከሀገሪቱ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ነው የተሰናዳው። ከጨዋታው ጎን ለጎን ነፃ የኤች አይ ቪ/ኤድስ ምርመራ እና የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብር እንደሚኖር ተነግሯል። በኢሜኑኤል አዲባየር ሀገር ቶጎ በደርሶ መልስ የተረቱት ኡጋንዳዎች ከምድብ አምስት አራት ነጥብ እና አንድ የግብ እዳ ይዘው በሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል፤ ምድቡን ጋና በስምንት ነጥብ ስትመራ ቶጎ በስድስት ነጥብ ትከተላለች።  ጊኒ በአራት ነጥብ እና በሶስት የግብ እዳ የመጨረሻውን ደረጃ ይዛለች። ስለሆነም ኡጋንዳ ወደ ቀጣይ ዙር የማለፍ እድሏን ለማስፋት ከጋና ጋር የምታደርገውን ጨዋታ ማሸነፍ ይጠበቅባታል። በማሊ በሜዳው 2 ለ 0 ተሸንፎ ባማኮ ላይ 3 ለ 2 ማሸነፍ የቻለውን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን መግጠም ከጋና ጋር ለሚያደርጉት ጨዋታ አቋማቸውን ለመፈተሽ እጅግ እንደሚጠቅማቸው ነው የኡጋንዳ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሚሉቲን ሰርዲዮቪች ሚቾ የተናገሩት። ምንጭ፦ www.fanabc.com

ኢትዮጵያ በኢቦላ ለተጠቁ ሀገራት 200 በጎ ፈቃደኛ ባለሙያዎችን ልትልክ ነው፤ በቫይረሱ ለተጠቁ ደግሞ ግማሽ ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ድጋፍ ለማድረግ ቃል ገባች ኣሉ

Image
ኢትዮጵያ በኢቦላ ለተጠቁ ሀገራት 200 በጎ ፈቃደኛ ባለሙያዎችን ልትልክ ነው፡፡ የጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ ዶክተር ከሰተብርሃን አድማሱ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፥ ኢትዮጵያ ባለሙያዎቹን የምትልከው የአፍሪካ ህብረት ሀገራት ኢቦላን ለመግታት በጎ ፍቃደኞችን እንዲልኩ ጥሪ ማቅረቡን ተከትሎ ነው ብለዋል፡፡ የባለሙያዎቹ ቡድን ሐኪሞችን፣ ነርሶችን፣ የፊልድ ኢፒዲሞሎጂ ባለሙያዎችን፣ የአካባቢ ጤና ባለሙያዎችንና የህብረተሰብ ጤና ስፔሻሊስቶችን ያካተተ ነው፡፡ ሚኒስትሩ እንዳሉት ከዚህ ቀደምም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ባደረገው ጥሪ መሠረት ከህብረቱ ቡድን ጋር የፊልድ ኢፒዲሞሎጂ ባለሙያዎች እንዲሳተፉ ተደርጓል፡፡  ይህ ድጋፍ አፍሪካዊ አንድነትና ትብብርን ከማጠናከሩም ባሻገር የዓለም አቀፍ ማህበረሰብን ካንዣበበበት አደጋ መታደግ መሆኑንም  ነው ዶክተር ከሰተብርሃን የተናገሩት፡፡ ኢትዮጵያ ቀደም ብሎ በአፍሪካ ህብረት ስር እንደዚህ ዓይነት በሽታዎችና ወረርሽኞች እንዳይከሰቱ ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያስችል ማዕከል እንዲቋቋም ሃሳብ ከማቅረብ ጀምሮ በትጋት እየሰራች ትገኛለችም ነው ያሉት፡፡  ይህ ዓይነት አዲስ የጤና ቡድን ድጋፍ ኢትዮጵያ ለአፍሪካ አንድነትና ጥንካሬ ያላትን የማያቋርጥ ቁርጥ አቋም የሚያሳይ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፥ ወደፊትም ድጋፉ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡ ዶክተር ከሰተብርሃን አክለውም ኢትዮጵያ በቫይረሱ ለተጠቁ ሀገራት ግማሽ ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ድጋፍ ለማድረግ ቃል መግባቷን ጠቁመዋል፡፡ በምዕራብ አፍሪካ እስካሁን ከ4 ሺህ 500 በላይ ሰዎች በቫይረሱ ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን፥ 9 ሺህ የሚሆኑ ሰዎች ደግሞ በቫይረሱ ተጠቅተዋል፡፡ ምንጭ፦  www.fanabc.com