Posts

በጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሰማራው ግዙፉ የአሜሪካ ኩባንያ ፒቪኤች ግሩፕ በሐዋሳ ከተማ የራሱን ፋብሪካ የማቋቋም ዕቅድ እንዳለው ተሰማ

Image
በጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሰማራው ግዙፉ የአሜሪካ ኩባንያ ፒቪኤች ግሩፕ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ የጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ ለመክፈትና ሩቅ ምሥራቅ የሚገኙ ደንበኞቹም ፋብሪካዎቻቸውን ወደ ኢትዮጵያ እንዲያዛውሩ ለማድረግ ከመንግሥት ጋር እየተደራደረ መሆኑን ምንጮች ገለጹ፡፡  ቶሚ ሂልፊገር፣ ካልቪን ክሊን፣ ቲምበርላንድና አይዞድ በሚባሉ የልብስ ብራንዶች የሚታወቀው ይህ ግዙፍ ኩባንያ፣ የደቡብ ክልል መቀመጫ በሆነችው ሐዋሳ ከተማ የራሱን ፋብሪካ የማቋቋም ዕቅድ እንዳለው ታውቋል፡፡ ኩባንያው ራሱ ከሚያቋቁመው ፋብሪካ በተጨማሪ፣ ሩቅ ምሥራቅ በሚገኙ አገሮች ልብስ አምራች ደንበኞቹ ፋብሪካቸውን ወደ ኢትዮጵያ እንዲያዛውሩ ፍላጎት አሳይቷል፡፡ የያዘውን ዕቅድ ለማሳካት በጉዳዩ ላይ ከመንግሥት ባለሥልጣናት ጋር እየመከረ መሆኑ ታውቋል፡፡ የኩባንያዎቹ የሥራ ኃላፊዎች ሰሞኑን አዲስ አበባ በመምጣት ድሬዳዋ፣ ሐዋሳና አዲስ አበባ የሚገኙ ኢንዱስትሪ ዞኖችን ጎብኝተዋል፡፡ በቆይታቸው ወቅት የተለያዩ የጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካዎችን ከመጎብኘታቸውም በተጨማሪ፣ ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝና ከኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ አብተው ጋር በወደፊት ዕቅዶች ላይ ምክክር አድርገዋል፡፡ ከኢትዮጵያ ጨርቃ ጨርቅና ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት የተገኘው መረጃ እንደሚያስረዳው፣ ፒቪኤች ግሩፕ በዓለም አቀፍ ደረጃ ትልቁ የአልባሳት ገዥና ሻጭ ነው፡፡ ኩባንያው ለደንበኞቹ የገንዘብ አቅርቦት ያመቻቻል፡፡ የኢትዮጵያ ጨርቃ ጨርቅና ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ማርኬቲንግ ኃላፊ አቶ ያሬድ መስፍን ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ኩባንያው 60 ሺሕ ሔክታር መሬት ለጥጥ ልማት ጠይቋል፡፡ ኢንስቲትዩቱ በጥጥ ልማት የሚሆን መሬት በደቡብ ክልል በማፈላለግ ላይ ነው ብለዋል፡፡  እ.ኤ.አ.

ሞሮኮ ኢቦላን በመፍራት የአፍሪካ ዋንጫን እንደማታዘጋጅ ተገለጸ

Image
ከወራት በኋላ የአፍሪካ ዋንጫን ለማዘጋጀት በዝግጅት ላይ የነበረችው ሞሮኮ ኢቦላ በአፍሪካ አህጉር እያሳየ የመጣውን ከፍተኛ መስፋፋት በመፍራት ራሷን ከአዘጋጅነት ማግለሏን ዘጋርድያን አስነበበ፡፡ ደቡብ አፍሪካ፣ ግብጽ፣ ጋና  ወይም ሱዳን ውድድሩን የማዘጋጀት ዕድል አላቸው ተብሏል፡፡ ሞሮኮ ከዚህ ውሳኔዋ በፊት የጨዋታው ጊዜ ይራዘምልኝ ጥያቄ ለካፍ ማቅረቧ ይታወሳል፡፡ ምንም እንኳ ካፍ ጥያቄውን ውድ ቢያደርገውም፡፡ ሞሮኮ አላዘጋጅም ማለቷን ተከትሎ ውድድሩ ወደ ሚቀጥለው ዓመት ይራዘማል፣ ወይም ደግሞ ውድድሩ ታጥፎ በጎርጎሮሲያኑ 2017 ሊካሄድ ይችላል ተብሏል፡፡ ሞሮኮ ለሀገሪቱ ዜጎች ሲባል ከአዘጋጅነቷ ራሷን ማግለሏን የሚገልጽ ዘገባ ሱፐር ስፖርት ባለፈው ማክሰኞ  የሀገሪቱን እግር ኳስ ፌደሬሸን በማነጋገር ያወጣውን ዘገባ ዘጋርዲያን እንደ ማስረጃነት አቅርቧል፡፡ በዘገባው የሞሮኮ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ሞሀመድ ኦዚኒ እንዳሉት   አሁን ታሪካዊ ሀላፊነት አለብን፣ በውሳኔው ካፍ ችግር እንደሚገጥመው እንገነዘባለን፣ ነገር ግን በታሪክ እንደዚህ ዓይነት መጥፎ በሽታ አጋጥሞን አያውቅም  ብለዋል፡፡ የ2013 የአፍሪካ ዋንጫ ያዘጋጀችው ደቡብ አፍሪካ ውድድሩን ወደ ሀገሯ ለመውሰድ ድርድር ላይ መሆኗን ዘገባው አስቀምጧል፡፡ የጋና ስፖርት ሚንስትርም ውድድሩን በሀገራቸው ለማዘጋጀት ጥያቄውን ለካፍ ለማቅረብ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል፡፡ ሞሮኮ ይህን ውሳኔ መወሰኗን ተከትሎ ካፍ ብሔራዊ ቡድኗንና ክለቦቿን ከውድድር እንደሚያግዳቸው ይጠበቃል፡፡ ሞሮኮ ኢቦላን በመፍራት የአፍሪካ ዋንጫን እንደማታዘጋጅ ተገለጸ ከወራት በኋላ የአፍሪካ ዋንጫን ለማዘጋጀት በዝግጅት ላይ የነበረችው ሞሮኮ ኢቦላ በአፍሪካ አህጉር እያሳየ የመጣውን ከፍተኛ

Boom times for Ethiopia's coffee shops

Image
Addis Ababa, Ethiopia Tomoca now has five cafes across Addis Ababa Continue reading the main story Entrepreneurship The man behind the eBay of Latin America Business loans for single mums 'Fancy a Snog?' Stalinism to start-ups Traditionally it takes rather a long time to be served a cup of coffee in Ethiopia - but things are now speeding up. As coffee plants originate from the east African nation - where they first grew wild before cultivation started in the country more than 1,000 years ago - it is perhaps unsurprising that Ethiopians take coffee drinking very seriously. So much so that Ethiopia has a ceremonial method of making coffee at home that continues to this day. The ceremony sees raw beans roasted over hot coals, with each person in attendance being invited to savour the smell of the fumes. The beans are then ground with a wooden pestle and mortar before finally being brewed - twice - in a clay boiling pot called a jebena. Continue reading the

AFcon 2015: Ethiopia defeats Mali 3-2 in Bamako

Image
Bamako, Mali -  The Ethiopian national team “Walias” achieved a surprising result here today when they beat Mali 3-2 to avenge their 2-0 defeat in Addis Ababa on Saturday. It was Mali who scored first through Bakary Sako (32″), but the Walias responded with 2 quick goals of their own by Omed Oukri (36′) and Getaneh Kebede (45′). The second half didn’t start well for the Walias as Getaneh Kebede was given his marching order (59″) to be followed by Mali equalizing in the 69th minute thanks to Mustaph Yattabare. It was Abebaw Butako who scored the winning goal for Ethiopia in extra time. http://www.ethiosports.com/2014/10/15/afcon-2015-ethiopia-defeats-mali-3-2-in-bamako/

የቀድሞው የቤቶች ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ተፈሪ ፍቅሬ ጥፋተኛ ተባሉ

Image
የቀድሞው የቤቶች ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ጥፋተኛ ተባሉ የተለያዩ የመንግሥት ቤቶችን የኪራይ ዋጋ በመቀነስና በዜጎች መካከል ልዩነት በመፍጠር፣ መንግሥት 370,476 ብር ጉዳት እንዲደርስበት ለማድረግ ሥልጣናቸውን ያላግባብ በመጠቀም የሙስና ወንጀል የተከሰሱት፣ የቀድሞ የመንግሥት ቤቶች ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ጥቅምት 4 ቀን 2007 ዓ.ም. ጥፋተኛ ተባሉ፡፡ ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ተፈሪ ፍቅሬ ጎሳዬ የፌዴራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ባለፈው ዓመት የመሠረተባቸውን ክስ ሲመረምር የከረመው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አንደኛ ወንጀል ችሎት ነው ጥፋተኛ የተባሉት፡፡ አቶ ተፈሪ በሥልጣን ላይ እያሉ፣ በቀድሞ ወረዳ 23 ቀበሌ 12 የቤት ቁጥር 106 የሆነውና በውጭ ምንዛሪ ተከራይቶ የነበረን ቤት፣ የኤጀንሲውን መመርያ አንቀጽ 13 (5) ውድቅ በማድረግ ለኢትዮጵያዊ ማከራየታቸው፣ በቀድሞ ወረዳ 21 ቀበሌ 01 የቤት ቁጥር 112/40 ባሰፋ ትሬዲንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር፣ ለንግድ በጨረታ አሸንፎ የነበረውን ቤት በመመሳጠር ወደ መኖሪያ ቤት በመቀየርና ኪራዩን በመቀነስ፣ በቀድሞ ወረዳ 18 ቀበሌ 05 የቤት ቁጥር 008/14 ውስጥ ተከራይ የነበሩትን የምክር ቤት አባል ከጠቅላይ ሚኒስትሩ የተጻፈ የድጋፍ ደብዳቤ ሳይኖር በመመሳጠርና በምክር ቤት አባላት ላይ ልዩነት በመፍጠር እንዲከራዩ በማድረግና ሌሎችንም ተጨማሪ ቤቶች ሥልጣናቸውን በመጠቀም ኪራይ ቀንሰው እንዲከራዩ በማድረግ በመንግሥት ላይ ጉዳት ማድረሳቸውን ክሱ ያብራራል፡፡ ከሳሽ ዓቃቤ ሕግ እንደ ክሱ የሰነድና የሰዎች ምስክሮችን በማቅረብ ለፍርድ ቤቱ ማስረዳቱን ፍርድ ቤቱ በብይኑ ገልጾ፣ አቶ ተፈሪ እንዲከላከሉ በማዘዝ ተከላክለዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ የሆኑት ዶ/