Posts

የዓለም ባንክ ኢትዮጵያ ለብድር ዕዳ አደጋዎች የመጋለጥ ዕድሏ እየሰፋ ነው አለ

Image
ሰሞኑን ለሦስት ቀናት ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩት የዓለም ባንክ ማኔጂንግ ዳይሬክተርና የኦፕሬሽን ዋና ኃላፊ ስሪ ሙሊያኒ ኢንድራዋቲ፣ እያደገ የመጣው የብድር ዕዳ መጠን በኢትዮጵያ ላይ አደጋዎችን ሊያስከትል እንደሚችል ገለጹ፡፡  ኢንድራዋቲ ባለፈው ረቡዕ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፣ ምንም እንኳን የአገሪቱ የብድር ዕዳ መጠን ከጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት አኳያ ያለው ድርሻ አነስተኛ ቢሆንም፣ የዕዳውን መጠን በግልጽነት ለማስተዳደር የሚችልና ግልጽነት የሰፈነበት አስተዳደር ማስፈን የመንግሥት ግዴታ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡  የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ይፋ ያደረገው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ አገሪቱ ያለባት ጠቅላላ የብድር መጠን 20 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል፡፡ ከዚህ ውስጥ 12 ቢሊዮን ዶላር ከውጭ ምንጮች የተገኙ ብድሮችን የሚሸፍን የዕዳ መጠን ነው፡፡ በዚህ መሠረት ከጠቅላላ አገር ውስጥ ምርት አኳያ የዕዳው ድርሻ 44 ከመቶ መድረሱን ይጠቁማል፡፡  ኢንድራዋቲ እንደሚገልጹት፣ ይህ አኃዝ ዝቅተኛ በሚባለው የዕዳ ደረጃ ላይ የሚገኝ ነው፡፡ ነገር ግን የመንግሥት የኢንቨስትመንት ወጪዎች እየተበራከቱ በመምጣታቸው ምክንያት የዕዳ መጠኑን በዚያው ልክ እያደገ በመሆኑ፣ የመንግሥት የልማት ድርጅቶችን በሚመለከት ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝና ከሚመለከታቸው ሚኒስትሮች ጋር መነጋገራቸውን አስረድተዋል፡፡ ከውይይቶቹ መካከልም በመንግሥት አስተዳደር ማሻሻያ ሪፎርሞች ላይ ያተኮረው አንዱ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ በዚህም መንግሥት በአስተዳደራዊ መዋቅሮቹ ላይ ማሻሻያ በማድረግ፣ ግልጽነትና ኢኮኖሚውን በብቃት የማስተዳደር ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡  የመንግሥት የልማት ድርጅቶች በየጊዜው እየጨመረ የመጣውን  የኢንቨስትመን

ኢትዮጵያና ሩሲያ ወታደራዊ ትብብራቸውን ለማጠናከር ተስማሙ

Image
-   ልዩ ኢኮኖሚያዊ ትብብሮችን ለማድረግም አቅደዋል ኢትዮጵያና ሩሲያ ለዓመታት የቆየ ትብብራቸውን በተለይም ወታደራዊ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ከመግባባት ላይ ደረሱ፡፡ ሁለቱ አገሮች የመግባባት ስምምነት ላይ የደረሱት የሩሲያው የረዥም ጊዜ ዲፕሎማትና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ሰርጌይ ላቭሮቭ ባለፈው ሐሙስ ለአንድ ቀን የሥራ ጉበኝት አዲስ አበባ በመጡበት ወቅት ነው፡፡ ሰርጌይ ላቭሮቭ በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በደረሱበት ወቅት የተቀበሏቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ናቸው፡፡ በመቀጠልም ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ በሁለቱ አገሮች የጋራ ጉዳይ ላይ ከሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር መክረዋል፡፡ ከሁለቱ አገሮች ባለሥልጣናት ምክክር በኋላ ለጋዜጠኞች የተካሄደው ውይይት የገለጹት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ሰርጌይ ላቭሮቭ፣ በተለያዩ የሁለቱ አገሮች የጋራ ትብብሮች ላይ መምከራቸውን፣ ከእነዚህም መካከል በወታደራዊ ትብብርና በልዩ ኢኮኖሚያዊ ግንኙነቶች ለመተባበር መግባባታቸውን ገልጸዋል፡፡ ባለፈው ሐምሌ ወር የሁለቱ አገሮች ከፍተኛ ባለሥልጣኖች በጋራ ኮሚሽን ስብሰባ ላይ ተገናኝተው በሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ በኢነርጂ፣ ተደራራቢ ግብርን ለማስቀረትና የኢንቨስትመንት ጥበቃ ለማድረግ መስማማታቸውን የገለጹት ሰርጌይ ላቭሮቭ፣ ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ጋር ተግናኝተው በተነጋገሩብት ወቅት የተጠቀሱት የትብብር መስኮች በፍጥነት እንዲተገበሩ ለማድረግ መስማማታቸውን አስረድተዋል፡፡ ይህ ሲባል ሌሎች ጉዳዮች የሉም ማለት እንዳልሆነ የተናገሩት ሚኒስትሩ፣ በተለይ የሁለቱ አገሮች ግንኙነት መገለጫ ባህሪ የሆነው ወታደራዊ ትብብር ተጠናክሮ እንዲቀጥል መስማማታቸውን አስታውቀዋል፡፡ ዶ/ር ቴድሮስ በበኩላቸው

የፌዴራል መንግስት መስሪያ ቤቶች ሲዳማን ኣይቀጥሩም እንዴ?

Image
በፌዴራል የመንግስት ተቋማት ውስጥ በተለያዩ የሙያ መስኮች ተቀጥረው በማገልግል ላይ ያሉትን የመንግስት ስራተኞች የብሔር ስብጥር በተመለከተ ሰሞኑ የወጣው ኣንድ መረጃ እንደምያመለክተው በኣገሪቱ በህዝብ ብዛት ኣምስተኛ ደረጃ ላይ ከምገኘው የሲዳማ ብሔር መሆናቸውን የገለጹ ተቀጣሪዎች ቁጥር ኣጠቃላይ ድምር 223 ብቻ ነው። ይህም ከመቶ ስሰላ ዜሮ ነጥብ 25 ነው። የዜናው ዝርዝር ከታች ይመልከቱ፦   This chart, sent to us by well placed source, shows ethnic composition of employees of Ethiopia’s  federal government. The data shows huge disparity when compared to ethnic composition of the country, even if we use the disputed 2007 census.   Amharas make up 51% percent of the employees, which is twice the size of their proportion of the country’s  population. Oromos make up 12.7% which is one-fourth of their population size. Somalis, the third largest ethnic group in the country,  make up about 6.2% of the total population but  they only constitute just 0.07% of the federal government’s workforce. There is a group categorized as ‘unidentified/ undisclosed’ constituting  23.7% of the federal workforce. While its not clear wha

Water to Djibouti and discourse with Egypt

Image
By Abebe Aynete,  What is new in resuming tripartite talks on an Ethiopian multi-billion dollar hydroelectric dam on the Nile after eight months of disruption? Indeed the three countries, Ethiopia, Egypt and Sudan have conducted talks from August 25-26 in Khartoum. The negotiation however, was suspended in January 2014 amid mounting tension between Cairo and Addis Ababa.   The  new development in the negotiation  has picked up where it left off at the time of its interruption, which is the formation of a committee for  implementing  the agreed proposal  involves a hydrology simulation model and a trans-boundary social, economic and environmental impact assessment. The negotiations resumed after Prime Minister Haile Mariam Dessalegn and Egyptian President Al-Sissi’s meeting during the 23rd African Union (AU) summit in Malabo, Equatorial Guinea.  As it is well known, it is not something new for Ethiopia and Egypt to undertake negotiations. What is new is that Egypt, which

የአፍሪካ እግር ኳስ ዋንጫ አዘጋጅ አገር ይፋ ሆነ

Image
አዲስ አበባ መስከረም 10/2007 የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌደሬሽን /ካፍ/ የ2019 ፣ የ2021 እና 2023 የአህጉሩን ዋንጫን ለማስተናገድ የተመረጡ አገሮች  ዛሬ ይፋ አደረገ። በዚህ መሰረት 2019 የአፍሪካ ዋንጫ  ለማዘጋጀት ካሜሮን፣2021 ኮትዲቯር፣የ2023 ደግሞ ጊኒ አንዲያዘጋጁ ተመርጠዋል፡፡ በትናንትናው ዕለት ዋንጫውን ለማስተናገድ ፍላጎት ያላቸው አገራት የማስተናገድ አቅም የሚያሳይ ፅሑፍና የ30 ደቂቃ ቪዲዮ በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ ለካፍ አመራሮች ቀርበዋል። አልጄሪያ፣ ካሜሮን፣ ጊኒ፣ ኮትዲቯርና ዛምቢያ ዋንጫውን ለማዘጋጀት አቅም እንዳላቸው የሚያሳይ ፅሑፍ ያቀረቡ  አገራት ናቸው።