የወንዶ ገነት ግብርና ምርምር ማእከል: ለምግብ መድሀኒትና ነዳጅ ዘይት በሚያገለግሉ እጽዋቶች ላይ ምርምር እያካሄደ ነው
ሻሸመኔ ጳጉሜ 5/2006 ኢትዮጵያ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የምታስገባውን መድሃኒት፣ምግብ ማቀነባበሪያ፣የኮስሞቲክስና ነዳጅ ዘይት ወጪ በሂደት ለማስቀረት ምርምር እያካሄደ መሆኑን የወንዶ ገነት ግብርና ምርምር ማእከል አስታወቀ። በማእከሉ የመአዛማ፣መድሃኒትና ነዳጅ ዘይት እጽዋቶች አስተባባሪና ተመራማሪ አቶ በእምነት መንገሻ ሰሞኑን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት ባለፉት አምስት ዓመታት ማእከሉ ምርምር ካካሄደባቸው 30 እጽዋቶች መካከል 20ዎቹ ለምግብ፣ለመጠጥ ማቀነባበሪያ፣ ለስኳር ፣ ለመድሃኒትና ነዳጅ ዘይት የሚያገለግሉ መሆናቸው በሙከራ ተረጋግጧል። ከውጪና ከሐገር ውስጥ አሰባስቦ ምርምር ያካሄደባቸውን እጽዋቶች በልማቱ ለሚሳተፉ አርሶ አደሮችና ባለሃብቶች ማሰራጨቱን ገልጸዋል። ማእከሉ ከንግድ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ባካሄደው የገበያ ጥናት መሰረት ሐገሪቱ ከውጭ ለምታስገባቸው የምግብ ማቀነባበሪያ፣መድሀኒትና ነዳጅ ዘይት ውጤቶች በየአመቱ ከሁለት ነጥብ አምስት ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር እንደምታወጣ መረጋገጡን አስታውቀዋል። ከጃትሮፋ ተክል ነዳጅ፣ከመአዛማ እጸዋቶች ኮስሞቲክስ፣የጸጉርና ገላ የውበትና ጤንነት መጠበቂያ፣ለመድሀኒት ቅመማ የሚያገለግሉ እጽዋቶች በምርምር ማግኘቱን ገልጸዋል። ማእከሉ ሐገሪቱ የምታወጣውን የውጭ ምንዛሪ ለማስቀረትና ምርቱን በማስተዋወቅ ለአለም አቀፍ ገበያ ለማቅረብ ለጀመረው ኢንዱስትሪ መር ስትራቴጂ እቅድ ነድፎ እየሰራ መሆኑንም አስታውቀዋል። የሚያፈልቃቸውን የምርምር ውጤቶች ለአርሶ አደሩና ባለሃብቱ በማስተዋወቅና በማሰራጨት ተጠቃሚው ህብረተሰብ ዘንድ እንዲደረስ ትኩረት መሰጠቱን ገልጸዋል። በሰው ሰራሽና በተለያየየ ምክንያት የተራቆተውን መሬት በማእዛማ እጽዋቶች ሸፍኖ የአፈር ለምነት