Posts

በርካታ የሲዳማ ባላሃብቶችን በሽርክና የያዘው ደቡብ ግሎባል ባንክ ኣዲስ ፕሬዚዳንት ልሾምለት ነው

Image
የአቢሲኒያ ባንክ ፕሬዚዳንት ቀጣይ ማረፊያ ደቡብ ግሎባል ባንክ እንደሆነ ተጠቆመ - ባንኩ ገንዘብና ወርቅ ሸልሞ ሸኛቸው    -    የደቡብ ግሎባል ባንክ ፕሬዚዳንት ከኃላፊነታቸው ለቀቁ በዳዊት ታዬ  ከአቢሲኒያ ባንክ ፕሬዚዳንትነታቸው በፈቃዳቸው መልቀቃቸውን ያሳወቁት አቶ አዲሱ ሃባ፣ ቀጣይ ማረፊያቸው ደቡብ ግሎባል ባንክ እንደሆነ ተጠቆመ፡፡ የደቡብ ግሎባል ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ ወርቁ ለማ ደግሞ ኃላፊነታቸውን ለቀዋል፡ ፡ አቢሲኒያ ባንክ ለአምስት ዓመት የመሩት አቶ አዲሱ፣ በባንኩ ታሪክ የመጀመሪያ ነው በተባለው የሽኝት ፕሮግራም ላይ፣ በባንኩ ቦርድ ውሳኔ መሠረት የግማሽ ሚሊዮን ብር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡  ከገንዘብ ሽልማቱ በተጨማሪ ለእርሳቸውና ለባለቤታቸው በነፍስ ወከፍ ሃያ ግራም ወርቅ የተበረከተላቸው ሲሆን፣ በቆይታቸው ለባንኩ ያበረከቱት አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደነበር የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀመንበር አቶ መሐሪ ዓለማየሁ በሽኝት ፕሮግራሙ ላይ ተናግረዋል፡፡  ቅዳሜ ነሐሴ 24 ቀን 2006 ዓ.ም. በሒልተን ሆቴል በተደረገው የሽኝት ፕሮግራም ላይ አቶ መሐሪ የአቶ አዲሱ መልቀቅ ድንገተኛና ያልተጠበቀ መሆኑን የገለጹት፣ ‹‹አቶ አዲሱ በራሳቸው ምክንያት ባንካችንን ለመልቀቅ ስለጠየቁ ቦርዱም ጥያቄው ድንገተኛ ሆኖ ደስተኛ ባይሆንም ጥያቄውን ተቀብሎታል፤›› በሚል ነው፡፡ አያይዘውም ከአቶ አዲሱ ጋር ወደፊትም መልካም ግንኙነቱ እንደሚቀጥል ያላቸውን ተስፋ ገልጸዋል፡፡ አቶ አዲሱ በአምስት ዓመት ቆይታቸው አበርክተዋል ያሉዋቸውን ዋና ዋና ተግባራት ያስታወሱት የቦርድ ሊቀመንበሩ፣ ‹‹አቶ አዲሱ ለአቢሲኒያ ባንክ የተቻላቸውን ሁሉ አድርገዋል ብዬ አምናለሁ፤›› ብለዋል፡፡ የደቡብ ግሎባል ባንክ ፕሬዚዳንትነታቸውን ያስረከቡት አ

ተቃዋሚ ፓርቲዎች ምን እየሆኑ ነው?

Image
ምርጫ 2007 ዘጠኝ ወራት ያህል እየቀሩት ነው፡፡ ይህ ወቅት ደግሞ የፖለቲካ ፓርቲዎች ዕጩዎችን የሚያዘጋጁበት፣ የምረጡኝ ቅስቀሳ ለመጀመር የቤት ሥራቸውን የሚያጠናቅቁበትና ምርጫው ምርጫ እንዲመስል የራሳቸውን ድርሻ የሚወጡበት ነው፡፡ አሁን እያየን ያለነው ግን ይህንን ምሥል ሳይሆን ተቃራኒውን ነው፡፡ የምርጫ ሸብ ረብ ሳይሆን በትንሽ በትልቁ እርስ በርስ መናቆር ነው፡፡ በሰላማዊ ትግሉ ውስጥ አለን የሚሉት ስማቸው ጎላ ብሎ የሚታይ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ሽኩቻ ውስጥ ናቸው፡፡ ከገዥው ፓርቲ ኢሕአዴግ ጋር ለዓመታት የከረሙበት መናቆር እንዳለ ሆኖ፣ አሁን ደግሞ ወደ ውስጥ ግብግብ ገብተዋል፡፡ የተቃዋሚ ፓርቲዎች መጠናከር ሳይሆን መፍረክረክ እየታየ ነው፡፡ ምርጫ ዋዜማ ላይ ሆኖ ይህንን ትርምስ የሚታዘቡ ደጋፊዎችም ሆኑ አባላት ተስፋ እየቆረጡ ይመስላል፡፡ የፖለቲካ ትግሉንም ሊሸሹ ይችላሉ፡፡ ይህ ደግሞ ለፖለቲካ ፓርቲዎች ህልውና አይበጅም፡፡ ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ በሚደረግ ሰላማዊ ትግል የፖለቲካ ፓርቲዎች ህልውና አስፈላጊ ነው፡፡ የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት የሚያብበው መራጩ ሕዝብ የተለያዩ አማራጮች ያሉዋቸውን ፓርቲዎች ማግኘት ሲችል ነው፡፡ አማራጭ ሲባል ለይስሙላ የሚነገር በጥናት ላይ ያልተመሠረተ ስንክሳር ሳይሆን በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚና በተለያዩ ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ የተደራጁ ፕሮግራሞችን ይዞ መቅረብ ነው፡፡ አሁን የምናየው ይህንን አይገልጽም፡፡ ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች ለእንቅስቃሴዎቻቸው መገደብ ሁለት ዓበይት ምክንያቶች አሉ፡፡ አንደኛው ውጪያዊ ሲሆን፣ ሁለተኛው ውስጣዊ ነው፡፡ ብዙ ጊዜ ውጫዊው ምክንያት በገዥው ፓርቲ ተፅዕኖ የሚገለጽ ነው፡፡ ይህ የፖለቲካ ምኅዳሩን ከማጥበብ አንስቶ በርካታ ምክንያቶች የሚቀርቡበት ተፅዕኖ ብዙ የተባለበት በመሆ

Sidaamu Fidalla

Image
የሲዳማን ቋንቋ ለየት ባለ መልኩ ማቅረብን ኣላማ ያደረገው ይህ መጽሐፊ በውስጡ 33 የሲዳሙኣፎ ፊደላቲን የያዘ ሲሆን፤ ከዚሁ ውስጥ 26 ቱ ነጠላ ኣሃዝ ፊደላቲ ሲሆኑ የተቀሩት 7 ቱ ደግሞ ባለ ሁለት ኣሃዝ ፊደላቲ ናቸው። መጽሐፉ 26 ቱ በላቲን ማለትም በእንግሊዥኛ እና በሌሎች ቋንቋዎች የሚገኙትን ፊደላቲ በቀላሉ ለመማር እንድያመች ዘንድ በፊደላቱ የሚጀምሩትን ቃላት በስዕል ኣስደግፎ ኣቅርቧል። በተጨማሪም የፊደላቱን የያዙ ቃላት በሲዳማ እና በኣፍሪካ ኣፌ ታሪኮች በማዋዛት በማይሰለች መልኩ ይተርካል። የተቀሩት ሰባቱ ለሲዳማ ኣፎ እንድመቹ ተደርገው የተቀረጹት፦ ch, dh, ny, ph, sh, ts እና zh የተባሉ ፊደላቲ በተመሳሳይ የመማሩን ህደት በሚያቀላጥፍ መልኩ ቀርበዋል። የመጽሐፉ የመጨረሻ ክፍል ደግሞ የሲዳማን የቀን፤ ሳምንት እና ወራት ኣቆጣጠርን በተመለከተ በማብራሪያ ኣስደግፎ ኣቅርበዋል። በኣጠቃላይ ይህ በካላ ጋልፋቶ ዎናጎ የተዘጋጀው የሲዳማ ፊደላቲ መጽሐፍ ፤ለሲዳማ ቋንቋ ጀማሪ ተማሪዎች ቋንቋውን በቀላሉ መማሪ እንድችሉ ከፍተኛ እገዛ የሚያድርግ ነው። መጽሐፉ በኣሁኑ ጊዜ በኣማዞን ደረ ገጽ ላይ በሽያጭ ላይ ይገኛል። የሲዳማን ቋንቋ ለመማሪ ለምፈልጉ ወዳጆች በሰጦታ መልክ ለማበርከት ኣልያም ለልጆቻችሁ ማስተማሪያነት መጽሐፉን መግዛት የምትሹ ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን መግዛት የምትችሉ መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን። ሲዳሙ ፊዳላ      

Doctors in Ethiopia are looking past their religious beliefs on abortions to save lives

Image
Credit:  Dalia Mortada 29-year-old Khadija Ali — a fake name she gave — had an abortion at Marie Stopes Clinic in Ethiopia. In Ethiopia, easier access to abortions has been one way the government has tried to save women’s lives. Since 2005, Ethiopia has made it much easier and cheaper for women to get legal abortions. It seems contrary to the population’s very conservative religious ideals, but doctors say they’re willing to look past their religion to save women’s lives.  In Ethiopia’s capital, Addis Ababa, many women come to the Marie Stopes Clinic to get birth control advice, to give birth and follow up on their pregnancies. Sometimes, they come to have abortions. That’s where 29-year-old Khadija Ali — a fake name she gave, because of the stigma associated with abortion — was undergoing an abortion. She says she’s not in too much pain. “I was working for a family in Bahrain where I was raped by my employer,” she explains, wringing her hands partly from anxiety, a

የሲዳማ ማክሮ ፋይናንስ ባለፉት 15 ኣመታት ተቀማጭ ካፒታሉን ከ200ሺ ብር ወደ ሁለት ሚሊዮን ዶላር ማሳደግ ብችልም፤ በዞኑ የማክሮ ፋይናንስ ገበያ ያለው ተወዳዳሪነት እየቀነሰ ነው

Image
እንደፈረንዶቹ ዘመን ኣቆጣጠር በ 1998 ኣመተምህረት ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ነገር ግን ሰርተው መለወጥ የምችሉ፤ በገጠር እና ከተማ ነዋሪ የሆነው እና ኣማራጭ የገንዘብ ተቋማት በኣቅራቢያቸው የሌሏቸው ዜጎች ለመረዳት ተብሎ በ 200 ሺ ብር ካፒታል የተቋቋመው የሲዳማ ማክሮ ፋይናንስ ባለፉት 15 ኣመታት ተቀማጭ ካፒታሉን ወደ ሁለት ሚሊዮን ዶላር ማሳደግ ብችልም፤ በዞኑ የማክሮ ፋይናንስ ገበያ ያለው ተወዳዳሪነት እየቀነሰ ነው። የማክሮ ፋይናሱ ኣሴት ( Assets) ባለፉት ኣስርተ ኣመታት ከ 2 ነጥብ 3 ሚሊዮን ዶላር ወደ 1 ነጥብ 9 ሚሊዮን ዶላር ወርዷል፤ የማክሮ ፋይናንሱ ኤኪቲይ ( Equity) ደግሞ ከ 1 ነጥብ 9 ሚሊዮን ዶላር ወደ 619 ሺ 085 ከ 06 ሳንቲም ወርዷል፤ ግሮስ ሎን ፖርትፎልዮ ( Gross Loan Portfolio) ደግሞ ከ 657 ሺ 678 ከ 99 ሳንቲም ወደ 2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ኣድጓል፤ ቀድሞ የሲዳማ ልማት ፕሮግራም በኃላ ላይ ደግሞ የሲዳማ ልማት ኮፕሬሽን እህት ኩባንያ ሆኖ በፍቃድ በቁጥር 40/1996 በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ቁጥጥር ስር ሆኖ የተመዘጋበው የሲዳማ ማክሮ ፋይናንስ በሲዳማ ዞን ውስጥ ባሉ የገጠር እና ከተማ ቀበሌያች የብድር ኣገልግሎት በመስጠት ላይ ሲሆን ወደ 50 ሺ የሚጠጉ የኣገልግሎቱ ተጠቃሚዎች እንዳሉት ታውቋል። ከኤም ኤፍ ኣይ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ማክሮ ፋይናንሱ እኣኣ በ 2012 ኣም 2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ግሮስ ሎን ፖርትፎሊዮ ሲኖረው፤ በኣማካይ 51 ነጥብ 8 ዶላር ማለትም ወደ ኣንድ ሺ ብር ለየኣንዳንዱ ተበዳር ኣበድሯል። የማክሮ ፋይናንሱ ከ 1 ነጥብ 3 ሚሊዮን ዶላር በላይ ተቀማጭ ገንዘብ ኣለው። ለ