ከዶ/ር አንበሴ ተፈራ የምርምር ስራዎች መካከል...
የኢትዮጵያ ብሔረሰቦችና ቋንቋዎቻቸው አጭር ቅኝት ( የዚህ አጭር ጽሁፍ አዘጋጅ ዶ/ር አንበሳ ተፈሪ ሲዳማ ውስጥ ይርባ በምትባል ቦታ በ1962 ተወለዱ።በ1984 ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ፡ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን፡ በ1987 ደግሞ ሁለተኛቸውን፡ በቋንቋ ጥናት ተቀበሉ።ከ1984 ጀምሮም፡ ወደ እስራኤል እስከተሰደዱበት 1990 ድረስ፡በተማሩበት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ውስጥ በመምህርነት አገልግለዋል።ከ1990 ጀምሮ ደግሞ በእስራኤል በተለያየ ቦታ በሚገኙ፡ ዩኒቨርስቲዎች፡እንዲሁም)የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ጭምር አማርኛንና የቋንቋ ጥናትን አስተምረዋል።መልካም ንባብ!) ኢትዮጵያ በተለምዶ 3 ሺ ዘመን ታሪክ ያላት ሲሆን በአንዳንድ ታሪካዊና የአርኪኦሎጂያዊ ቁፋሮ መረጃዎች ግን ይህ ታሪካዊ ዕድሜ እስከ 5 ሺ ዓመት ሊደርስ ይችላል። ይህቺ ረጅም ታሪክ ያላት አገር በአሁኑ ጊዜ በኦፊሲዬላዊነት 73 “በሕይወት ያሉ” ቋንቋዎች አሏት። የኢትዮጵያ 73 ቋንቋዎች የሚመደቡት በ2 የቋንቋ ቤተሰቦች ውስጥ ነው።እነዚህም አፍሮ-እስያዊ እና ኒሎ-ሰሐራዊ (ዓባይ-ሰሐራዊ) ናቸው። አፍሮ እስያዊ ቋንቋዎች በሰሜን አፍሪቃና በደቡብ ምዕራብ እስያ የሚነገሩ ሲሆን 6 ንዑሳውያን ቤተሰቦች አሉት። እነዚህም ጥንታዊ ግብጽ፣ በርበር፣ ቻዳዊ፣ ኩሻዊ (ሐማዊ)፣ ኦሞአዊና ሴማዊ ቋንቋዎች ናቸው። ከእነዚህ ከላይ የተጠቀሱት ውስጥ 3ቱ ማለትም ጥንታዊ ግብጽ፣ በርበር እና ቻዳዊ በኢትዮጵያ የማይነገሩ ሲሆን የተቀሩት 3ቱ ደግሞ ኢትዮጵያ ውስጥ ይነገራሉ። እነዚህም ኩሻዊ (ሐማዊ)፣ ኦሞአዊና ሴማዊ ቋንቋዎች ናቸው። በዕድሜ ረገድ ኩሻዊና ኦሞአዊ ጥንታዊ ቋንቋዎች ሲሆኑ ሴማዊ ቋንቋዎች ከእነሱ ቀጥለው ወደ ኢትዮጵያ የገቡ ናቸው። ሴማዊ ቋንቋዎች የሚባሉት ግዕዝ