Posts

የመንግስት ሰራተኞች የደሞዝ ጭማሪ መጠን እስካሁን አልታወቀም

በየ3 አመቱ የደሞዝ ጭማሪ ሊደረግ ይችላል ከመጪው ሐምሌ ወር ጀምሮ ለመንግስት ሠራተኞች እንደሚጨመር የተነገረው የደሞዝ መጠን እስካሁን በይፋ አልተገለፀም፡፡   በሌላ በኩል ከአሁን በኋላ በየሦስት አመቱ ለመንግስት ሠራተኞች የደሞዝ ጭማሪ ሊደረግ እንደሚችል ምንጮች ጠቁመዋል፡፡  በሲቪል ሠርቪስ ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ጌታቸው አብዲሣ፤ በቅርቡ መንግስት ይጨመራል ብሎ ከሰጠው መረጃ ውጪ በምን ያህል ፐርሰንት እንደሚጨመር መረጃ አልደረሰንም ብለዋል፡፡  ለመንግስት ሠራተኞች ለመጨረሻ ጊዜ ደሞዝ የተጨመረው በታህሳስ ወር 2003 ዓ.ም ሲሆን በወቅቱ ከ38.75 በመቶ እስከ 44.71 በመቶ የሚደርስ ጭማሪ መደረጉ የሚታወስ ሲሆን አሁን ከዚያ በላይ የደሞዝ ጭማሪ እንደሚጠበቅ በግል ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ መምህር አቶ መስፍን ይልማ ግምታቸውን ሰንዝረዋል። የደሞዝ ጭማሪው በተለይ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የመንግስት ደሞዝተኞችን ተጠቃሚ ማድረግ እንዳለበት ተናግረዋል - ምሁሩ፡፡  የደሞዝ ጭማሪ ስሌቱ አለመታወቁ ትንታኔዎችን ለመስጠት ያስቸግራል ያሉት መምህሩ፤ እስከዛሬ በመንግስት በኩል የሚደረጉ የደሞዝ ጭማሪዎች የሠራተኛውን ፍላጐት አርክተው አያውቁም፤ ይኸኛውም ጭማሪ የተለየ ነገር ይዞ አይመጣም ብለዋል፡፡  ባለፉት አምስት ዓመታት በፓርላማ ብቸኛ የተቃዋሚ ፓርቲ ተወካይ የሆኑት የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉ በበኩላቸው፤ የደሞዝ ጭማሪው አስፈላጊና ወቅታዊ መሆኑን ጠቅሰው፤ ጭማሪው አንዲት ሣንቲም እንኳ ቢሆን በሠራተኛው ህይወት ላይ ለውጥ ባያመጣም ትርጉም አለው ይላሉ፡፡  መንግስት መቼውንም ቢሆን የሠራተኛውን ፍላጐት ሊያሟላ የሚችል ደሞዝ የመጨመር አቅም አይኖረውም ያሉት የፓርላማ አባሉ፤ አንድ የመንግስት ሰራተኛ የሚመራው ኑሮ ሊስትሮ ከሚሰራ ሰው

የዲያስፖራውን ሙሉ መረጃ አጠናቅሮ መያዝ የሚያስችል አሰራር መዘርጋት ይገባል-ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

Image
አዲስ አበባ ሰኔ 23/2006 ዲያስፖራው በአገሩ የልማት እንቅስቃሴ ላይ በስፋት እንዲሳተፍና በሚኖርበት አገር ሁሉ መብቱን ማስከበር እንዲችል የዲያስፖራውን ሙሉ መረጃ አጠናቅሮ መያዝ የሚያስችል አሰራር መዘርጋት እንዳለበት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከአለም አቀፍ የስደተኞች ተቋም ጋር በመተባበር ከ20 በላይ ከሚሆኑ ኤምባሲዎች ለተውጣጡ የኢትዮጵያ አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች "ዲያስፖራውን ማወቅ" በሚል ርዕስ በአዲስ አበባ ስልጠና እየሰጠ ነው። በዚሁ ወቅት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ደዋኖ ከድር እንደተናገሩት የዲያስፖራውን ሙሉ መረጃ በማወቅ በአገሩ ልማት ላይ በስፋት እንዲሳተፍ ማድረግ ይገባል። ከአሁን በፊት የነበረው አሰራር የዲያስፖራውን መገኛ ቦታ ብቻ በማወቅ ላይ የተመሰረተ እንደነበር ጠቁመዋል፡፡ አቶ ደዋኖ እንዳሉት ዲያስፖራውን ከአገሩ ልማት ጋር ማቆራኘት እንዲቻል የአሁኑ ስልጠና ጥሩ ተሞክሮ ያላቸው አገሮችን ልምድ ያካተተ እንዲሆን ተደርጓል። ለአሁኑ ስልጠና እንዲሳተፉ የተጋበዙ ዲፕሎማቶች ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በስፋት ከሚገኙበት አገራት እንደመሆኑ መጠን ስልጠናውን ጨርሰው ወደመጡባቸው አካባቢዎች ሲመለሱ ዲያስፖራውን በማስተሳሰሩ ረገድ ብዙ ስራ ይጠብቃቸዋል ብለዋል። የአለም አቀፍ የስደተኞች ድርጅት ተልዕኮ የኢትዮጵያ ኃላፊ ሚስተር ጆሲያህ ኦጊና እንዳሉት ድርጅቱ የምሁራንን ፍልሰት ለመግታትና የስደተኞችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከመንግስት ጎን ይሰለፋል።   ከውጭ ለሚመለሱ ኢትዮጵያውያንም አጫጭር ስልጠናዎችን በመስጠት በዘላቂነት ራሳቸውን እንዲችሉ በማገዝና ጊዜያዊ የቁሳቁስ አቅርቦት በማድረግ ድጋፍ እንደሚያደርግም ገልፀዋል። ዲያስፖራው ለአገሩ ልማት

Your Fair Trade Coffee and Quinoa Aren’t Improving Farmers’ Lives

Image
When confronted with the ability to make the “ethical” choice at the grocery store, picking up a bag of Fair Trade certified coffee seems like a no-brainer. With a commitment to worthy goals like reducing poverty, empowering women, and supporting education, Fair Trade products appear to put the power of creating a better world in the hands of the purchaser. But the impact may not be a benefit for the poorest workers, and like other food trends, could be negatively impacting the lives of the people producing some of our foods. A recently released four-year study,  Fairtrade, Employment and Poverty Reduction in Ethiopia and Uganda , found that Fair Trade certification does not have the positive impact on producers consumers may believe it does. For the report, the University of London researchers collected data from Ethiopia and Uganda in regions where coffee, tea, and flowers are produced. It found that the workers involved in Fair Trade production had very low wages, and they did

Speech Recognition System: Speaker Dependent Recognizer for Sidama Language

Image
by  Abdella Kemal Mohammed   (Author) Speech recognition systems have been applicable in wide areas as various speech recognition methodologies, techniques and tools have been developed and implemented to generate a natural and intelligible speech. In this regard, this work attempts the possibility of developing a prototype speech recognition system for Sidama language using Hidden Marcov Model. The study has conducted extensive study on the language features, the components, speech recognition tools; the techniques used in speech recognition design, and identified those component that are dependent on the characteristics of language. Finally this work has showed a working prototype speech recognizer for the language, tested the performance of the system and compared its accuracy, and recommended measures for similar researches and projects. This work, therefore, will be useful to researchers, Speech application developers, Educators and other individuals or institutions working on

የቡና ንግድ ቀይ መብራት በርቶበታል

Image
ሚኒስትሮች ተሰብስበዋል፡፡ የሚኒስትሮቹ ጠቅላይ አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ስብሰባውን ይመራሉ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ ሚኒስትሮችና ከዚያ በታች በተዋረድ የሥልጣን ዕርከን ላይ የሚገኙ 37 ሹማምንት ለስብሰባው ሲጠበቁ 25ቱ ተገኝተዋል፡፡ በሦስት ሚኒስቴሮች የኤክስፖርት አፈጻጸም ላይ በብሔራዊ ኤክስፖርት አስተባባሪውና የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ ሚኒስትር በአቶ አርከበ ዕቁባይ (የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ይዘዋል) ጠሪነት ለአምስት ሰዓት የዘለቀ ስብሰባ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽሕፈት ቤት ተካሂዷል፡፡ ስብሰባው ከጥቂት ወራት በፊት የተካሄደ ነው፡፡ ከመነጋገሪያ ነጥቦቹ አንዱ የሆነው የንግድ ሚኒስቴር የኤክስፖርት አፈጻጸም ነበር፡፡ ከዚህም ውስጥ ቡና ላይ ትኩረት አድርጎ፣ ሌሎች የግብርና ምርቶችንም ተመልክቷል፡፡ ‹‹በንግድ ሚኒስቴር ክትትል የሚደረግባቸው የግብርና ምርቶች የኤክስፖርት ዕቅድ አፈጻጸም በተያዘው ዕቅድ መሠረት ለማሳካት የተከተልነው የአሠራር ሥርዓትና የማኔጅመንት አመራር ለውጥ ያላመጣው በምን ምክንያትን እንደሆነ አጽንኦት ተሰጥቶት ቢታይ፤›› የሚል መነሻ ያሰፈረው የመወያያ አጀንዳ፣ ከዚህ ቀደም በኤክስፖርት ብሔራዊ አስተባባሪ ኮሚቴው በኩል የተሰጡ ማሳሰቢያዎችና የሥራ መመርያዎች ብዙም ለውጥ እንዳላመጡ ይገልጻል፡፡  ከቀረቡት ዝርዝር ነጥቦች መካከል ለአብነት መጥቀስ ቢያስፈልግ፣ ከዚህ ቀደም ኮሚቴው የኢትጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን፣ የንግድ ሚኒስቴር፣ የግብርና ሚኒስቴርና የፀጥታ አካላት በጋራ ተቀናጅተው በተለይ የቡና ኤክስፖርት ዕቅድ አፈጻጸምን ለማቀላጠፍ ይቻል ዘንድ፣ ቡና በብዛት ወደ ምርት ገበያ እንዲገባ በማድረግ የአቅርቦት መጠኑ እንዲጨምር የሚል መመርያ ሰጥቶ እንደነበር ያስታውሳል፡፡ ሆኖም ግን የተለየ ለውጥ አለመምጣቱን