Posts

የጉምሩክ አዋጅ ሊሻሻል ነው

-  ክስ የማይመሠረትባቸው የጉምሩክ ጥፋቶች ተዘርዝረዋል     -  የምርት ሒደታቸውን ባላጠናቀቁ ምርቶች ላይ የቀረጥ ነፃ አሠራር ይፈቅዳል      -   ዋና ዳይሬክተሩ ክስ አለመመሥረት የሚችልባቸው አሠራሮች ተቀምጠዋል በ2001 ዓ.ም. ፀድቆ ሥራ ላይ የዋለውን የጉምሩክ አዋጅ የሚያሻሽልና የአገሪቱን የማኑፋክቸሪንግ ዘመቻ የመደገፍ ግብ የያዘ የጉምሩክ ማሻሻያ አዋጅ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀረበ፡፡ አዋጁ ለአገር ውስጥ ፍጆታ የሚውሉ የምርት ሒደታቸውን ያላጠናቀቁ ምርቶች ከቀረጥ ነፃ ገብተው በጉምሩክ ቁጥጥር ሥር የምርት ሒደታቸውን እንዲያጠናቅቁ ይፈቅዳል፡፡ ምንጭ በአገሪቱ እየታየ ያለው የኢኮኖሚ ዕድገት የሚጠይቀው የጉምሩክ አሠራርን ማካተት አስፈላጊ መሆኑን መንግሥት ስላመነበት ማሻሻያ ረቂቁ መዘጋጀቱን፣ ባለፈው ሐሙስ ለፓርላማ የቀረበው የአዋጁ ማብራርያ ይገልጻል፡፡ አዋጁን ለማሻሻል ምክንያት ከሆኑት መካከል የወጪና ገቢ ንግድ ዕድገት፣ በተለይም የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ልማት የሚጠይቃቸውን ቀልጣፋ የጉምሩክ አገልግሎት ለመስጠትና የተመጣጠነ ቁጥጥር ለማድረግ የሚያስችሉ አሠራሮችን ሥራ ላይ ለማዋል፣ ዘመናዊና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ያገኙ የጉምሩክ አሠራሮችን ለማስፈጸም የሚያስችል ሕግ ማውጣት አስፈላጊ መሆኑ ይገኙበታል፡፡ አዋጁ ካካተታቸው ዋና ዋና ለውጦች መካከል የምርት ሒደታቸውን ሳያጠናቅቁ ወደ አገር የሚገቡ ዕቃዎች ያለቀረጥ የሚስተናገዱበትና በጉምሩክ ቁጥጥር ሥር የሚጠናቀቁበት አሠራር አንዱ ነው፡፡ ይህ አሠራር ከውጭ አገር የመጡ ዕቃዎች ለአገር ውስጥ ፍጆታ ከመለቀቃቸው በፊት አገር ውስጥ የምርት ሒደታቸውን የሚያጠናቅቁበትና ለአገር ውስጥ ፍጆታ ሲለቀቁ ቀረጥና ታክስ እንዲከፈልባቸው የሚደረግበት አሠራር መሆኑን የ

Ethiopia ranks second poorest country in the world - Oxford University Study

nazret.com - According to The Global Multidimensional Poverty Index (MPI), published by  Oxford University , Ethiopia ranks the second poorest country in the world just ahead of Niger. The study is based on analysis of acute poverty in 108 developing countries around the world. Despite making progress at reducing the percentage of destitute people, Ethiopia is still home to more than 76 million poor people, the fifth largest number in the world after India, China, Bangladesh and Pakistan. India has the world's largest number of poor people at more than 647 million. 87.3% of Ethiopians are classified as MPI poor, while 58.1% are considered destitute. A person is identified as multidimensionally poor (or 'MPI poor') if they are deprived in at least one third of the weighted MPI indicators. The destitute are deprived in at least one-third of the same weighted indicators, The Global MPI uses 10 indicators to measure poverty in three dimensions: education, health and living

የሃዋሳ ከተማ የወደፊት እጣፋንታ ከወዲሁ ለመገመት እንዲያስችሎት

Image
...  በአገሪቱ ያልተማከለና የተመጣጠነ የከተሞች ዕድገትን ለማረጋገጥ ዘጠኝ የከተማ ዕድገት መሰላሎችና ዞኖች በአዲስ አበባ፣ በመቐለ፣ በባህር ዳር፣ በነቀምቴ፣ በወልዲያ/ኰምቦልቻ፣ በጅማ፣ በድሬዳዋ፣ በሐዋሳና በጐዴ እንደሚፈጠሩና የአዲስ አበባና የኦሮሚያ ልዩ ዞን ስኬት ለእነዚህ ስምንት ከተሞች እንደ መልካም ተሞክሮም እንደሚያገለግል መረጃው ያመለክታል፡፡... የሃዋሳ ከተማ የወደፊት እጣፋንታ ከወዲሁ ለመገመት እንዲያስችሎት  የሚከተለውን ጽሑፍ ያንቡ፦ የተቀናጀው ማስተር ፕላን በልማትና በፖለቲካዊ ጥያቄዎች መካከል ባለፈው ሳምንት ግንቦት 30 ቀን 2006 ዓ.ም. የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፌዴራሊዝም ጥናት ማዕከልና የደቡብ አፍሪካው ዌስተርን ኬፕ ዩኒቨርሲቲ በመተባበር ያዘጋጁት ሴሚናር በከተሞች አስተዳደር ላይ ያተኮረ ነበር፡፡ የሴሚናሩ ተሳታፊዎች ከምሁራን፣ ከመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ ከኦሮሚያ፣ ከአዲስ አበባና ከፌዴራል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ ከፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት፣ ከተለያዩ የጥናትና ምርምር ተቋማት ተወካዮች፣ ከፌዴራሊዝም ተማሪዎችና ከሌሎች የሚመለከታቸው አካላት የተውጣጡ ነበሩ፡፡ ከላይ የተገለጸው ሴሚናር ከመካሄዱ ከሁለት ቀናት በፊት የአዲስ አበባና በአዲስ አበባ ዙሪያ የኦሮሚያ ልዩ ዞን የተቀናጀ ማስተር ፕላን ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ለውጭ ሚዲያዎችና በእንግሊዝኛ ቋንቋ ለሚሠሩ ሚዲያዎች በማስተር ፕላኑ የዝግጅት ሒደት ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጠ ሲሆን፣ በጽሕፈት ቤቱ ዳይሬክተር በአቶ ማቴዎስ አስፋው የተመራው ቡድን አዲስ አበባንና ኦሮሚያን የወከሉ ኃላፊዎችን አካቶ ለተለያዩ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ሞክሯል፡፡ በሁለቱ ቀናት ዝግጅቶች ትኩረት የሳበው አጀንዳ የአዲስ አበባና የኦሮሚያ ክልል ግንኙነት ነው፡

ችግር ለሚፈጥሩ ቡና ላኪዎች የሥነ ምግባር ደንብ ተዘጋጀ

Image
ችግር የሚፈጥሩ የቡና ነጋዴዎች አደብ እንዲገዙ ያደርጋል የተባለ የሥነ ምግባር ደንብ ተዘጋጀ፡፡ ደንቡን ያዘጋጀው የኢትዮጵያ ኮፊ ኤክስፖርተርስ አሶሴሽን ሲሆን፣ ማኅበሩ በዚህ ሳምንት በጠራው ጠቅላላ ጉባዔ ደንቡን ያፀድቀዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ምንጮች ገልጸዋል፡፡  የተዘጋጀው የሥነ ምግባር ደንብ በተለይ ከውጭ አገር ገዥዎች ጋር የገቡትን የቡና ሽያጭ ስምምነት ውል የማያከብሩ ነጋዴዎች በአገሪቱ ቀጣይ የቡና ግብይት ላይ ሳንካ የሚፈጥሩ የቡና ኤክስፖርተሮችን ከጨዋታ ውጭ እንዲሆኑ ማድረግ የሚያስችል ዕርምጃ ለመውሰድ ከማስቻሉም በተጨማሪ፣ የሥነ ምግባር ችግር አለባቸው ተብለው የተፈረጁ ኤክስፖርተሮችን ጥቁር መዝገብ ውስጥ ያሳፍራል ተብሏል፡፡ የኢትዮጵያ ቡና ላኪዎች ማኅበር ከሌሎች አገሮች የቡና ላኪ ማኅበራት፣ በአፍሪካና በዓለም አቀፍ ደረጃ ከተቋቋሙ የቡና ማኅበራት ጋር ግንኙነት ያለው በመሆኑ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ጥቁር መዝገብ ውስጥ የገባ የቡና ኤክስፖርተር እነዚህ ተቋማት በሙሉ እንዲያውቁት ይደረጋል ተብሏል፡፡  ይህም አጥፊ ከተባለው ኤክስፖርተር ጋር ቀጣይ ግብይት ማድረግ አደጋ እንደሚመጣ ጠቋሚ በመሆኑ የተፈረጀው ላኪ ችግር ውስጥ ይወድቃል ተብሏል፡፡ ማኅበሩ ጥቁር መዝገብ ውስጥ ያሰፈረው ቡና ላኪ በመንግሥት በኩልም ምርመራ ተካሂዶበት ለቅጣት እንደሚዳረግም ተገልጿል፡፡ በማኅበሩ የተዘጋጀው የሥነ ምግባር ደንብ የንግድ ሚኒስቴር፣ ግብርና ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ምርት ገበያን ጨምሮ የተለያዩ የሚመለከታቸው አካላት አስተያየት እንዲሰጡበት ተደርጎ፣ የሰጧቸው አስተያየቶችም ተካተው የመጨረሻው ረቂቅ ተዘጋጅቷል፡፡  ነገር ግን የሥነ ምግባር ደንቡን በጥርጣሬ የሚመለከቱ ኤክስፖርተሮችም አሉ፡፡ እነዚህ ኤክስፖርተሮች እንደሚሉት፣ በሥነ ምግባር ደንቡ

የኮሪያ መንግሥት ለሞጆ-ሐዋሳ የፍጥነት መንገድ የፈቀደው ብድር ለፓርላማ ቀረበ

ከሞጆ-ሐዋሳ የመጀመሪያ ዙር የፍጥነት መንገድ ግንባታ የኮሪያ መንግሥት ኤግዚም ባንክ የፈቀደው 100 ሚሊዮን ዶላር ብድር ለፓርላማ ቀረበ፡፡ የሞጆ-ሐዋሳ መንገድ 201 ኪሎ ሜትር ርዝመት ሲኖረው፣ ግንባታው በሁለት ዙር ተከፍሎ የሚገነባ ነው፡፡ የጀመሪያው ዙር ግንባታ ከሞጆ-ዝዋይ በራሱ በሁለት ተከፍሎ የሚገነባ መሆኑን የብድር ማፅደቂያ አዋጁ አባሪ ሰነድ ያብራራል፡፡ የመጀመርያው ዙር የመጀመርያ ምዕራፍ ከሞጆ-መቂ ሲሆን፣ ለዚህ ግንባታ ማስፈጸሚያ የሚውል 128 ሚሊዮን 460 ሺሕ ዶላር በዚህ ዓመት ከአፍሪካ ልማት ባንክ መገኘቱን ሰነዱ ያብራራል፡፡ ለቀሪው የመቂ-ዝዋይ መንገድ ግንባታ ደግሞ የኮሪያ ኤክስፖርት ኢምፖርት (ኤግዚም) ባንክ 100 ሚሊዮን ዶላር መፈረሙን የአዋጁ አባሪ ይገልጻል፡፡ ከሞጆ-ሐዋሳ ድረስ የሚገነባው የፍጥነት መንገድ በአንድ ጊዜ አራት ተሽከርካሪዎችን እንዲያስተናግድ ይፈለጋል፡፡ አጠቃላይ ወጪውም 349 ሚሊዮን 480 ሺሕ ዶላር መሆኑን ሰነዱ ይገልጻል፡፡  ከኮሪያ መንግሥት የተገኘው 100 ሚሊዮን ዶላር የ15 ዓመት የችሮታ ጊዜን ጨምሮ በ40 ዓመት ጊዜ ውስጥ ተከፍሎ የሚጠናቀቅ ነው፡፡ ለፕሮጀክቱ ትግበራ ባንኩ በሚፈጽመው ክፍያ ላይ 0.1 በመቶ የአገልግሎት ክፍያ ከብድሩ ገንዘብ ላይ ተቀንሶ እንደሚከፈል፣ ጥቅም ላይ ባልዋለውና ባልተከፈለው የብድር ገንዘብ ላይ ደግሞ 0.01 በመቶ ወለድ እንደሚታሰብበት ረቂቅ ማፅደቂያ አዋጁ ይገልጻል፡፡ የብድር ስምምነቱ እስከዛሬ ከነበሩት የብድር ዓይነቶች ጋር ሲነፃፀር የ55 ዓመት መሆኑ፣ የአገልግሎት ክፍያውና ወለዱ በጣም ዝቅተኛ መሆኑ የፓርላማው አባላትን አስደንቋል፡፡ ‹‹የኮሪያ ኤግዚም ባንክ ብድር ሳይሆን ስጦታ ነው የሰጠው፤›› ሲሉ የምክር ቤቱ ዶ/ር አድሃና ኃይሌ አድንቀውታ