Posts

ፕሪሚየር ሊጉ ዛሬ በተለያዩ ጨዋታዎች ይቀጥላል

Image
ምንጭ፦ www.fanabc.com አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 23 ፣ 2006 ( ኤፍ.ቢ.ሲ. ) 22ተኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ በሚደረጉ የተለየዩ ጨዋታዎች ይቀጥላል። መከላከያ ከሀዋሳ ከነማ 9 ሰዓት ላይ ሲጫወቱ ፤ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከደደቢት 11 ሰዓት ከ30 ላይ በተመሳሳይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ይገናኛሉ። በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ደግሞ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከኢትዮጵያ መድህን 10 ሰዓት ላይ ይጫወታሉ። በክልል ከተሞች ዳሸን ቢራ ከወላይታ ዲቻ ፣ ሙገር ሲሚንቶ ከመብራት ሃይል ፣ ሀረር ቢራ ከኢትዮጵያ ቡና ፣ አርባ ምንጭ ከነማ ከሲዳማ ቡና በተመሳሳይ 9 ሰዓት ላይ ይገናኛሉ።

ሀዋሳ ቤሌማ……!

Image
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ኣርት “መጓዝ ማወቅ ነው…..!” ፡፡ እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር በ1995 ዓም (ከአስር ዓመት በፊት መሆኑ ነው) በወርሃ መስከረም ላይ በአሁን ሰዓት ላይ የደቡብ ብሄር ብሄረሰቦች ክልል በዋና ከተማነት የምታገለግለውን ሃዋሳ ከተማ ለመጀመርያ ጊዜ ለማየት በቃሁ…..፡፡ በሃይቁ ላይ በነጻነት የሚደንሱ የተለያዩ አሶች፤ደስ በሚለው የማያቃጥለው ሞቃት አየሯ እና ሰማይ ላይ በደስታ የሚንሳፈፉ የተለያዩ አእዋፋት……! ባላቸው አቅም ሁሉ በፍቅር አና በደስታ እንግዶቿን የሚያስተናግዱ ህዝቦቿ ልብ የሚመስጥ ነበር…..፡፡ በዚያን ጊዜ ከተማዋ አቅም እንደሌለው…. ወላጅ  እንደረሳው…. የህጻን ልጅ ቁምጣ እዚም እዛም የተቦጨቀ የአስፋልትና የጠጠር መንገዶች፤በአሁን ሰዓት መሃል ፒያሳ ጎዳናን በኩራት ተኮፍሶ የሚታየውን የገብርኤል ቤተክርስቲያን ጨምሮ በጅምር የቀሩ ጥቂት ህንጻዎች፤የሃዋሳ ሃይቀርን ተከትለው እንደሚታዩት ግዙፍ የሾላ ዋርካ ዛፎች….እድሜ የጠገቡ አብዛኛውን አሮጌ ቤቶችና የቆዩ ትንንሽ ሆቴሎች…..ወዘተ…. የነበራት ሃዋሳ…. ውበትዋ ማርኮኝ ከዛን ጊዜ ጀምሮ ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ እየተመላለስኩ ደስታዬን አጣጥሜያለሁ……!፡፡ እነሆ ዛሬ ከሁለት አመት ቆይ በኋላ ዳግም ተመልሼ እዛው እገኛለሁ ፡፡ እጅግ በሚገርም ሁኔታ ከተማዋ ተለውጣለች… አምራለች…!፡፡ በየጊዜው ለውጥ አለ የተጀመሩ ህንጻዎች አልቀው ሌሎች ተጀምረዋል፡፡በ1960ዎቹ አካባቢ 6ኪሎ ሜትር ብቻ ይሸፍን የነበረው የአስፋከልት መንገድ ዛሬ 56.6 ኪሎ ሜትር ደርሷል፡፡ ትንሽ የነበረው ወስጥ ለውስጥ የተቦዳደሰ መንገዶችዋ ዛሬ በኮብል ድንጋይ 18 ኪሎሜትር ያህል ተነጥፏል፡፡ ከሌሎች መሰል የሃገራችን ከተሞች በአንጻራዊነት ሲታይ በእድሜ ትንሽ ብትሆንም ተፈጥሮም እያገዛት እጅግ በፍጥነ

የኢህአዴግ 1 ለ 5 አደረጃጀት፣ ቀጣዩ ምርጫ እና የተቃዋሚዎች ስጋት

“በልማት ሰበብ አፈና የሚፈፀምበት መዋቅር ነው” - መኢአድ “1ለ5 አደረጃጀት ለምርጫው ስጋት አይሆንም”  - አንድነት “ፓርቲያችን፤ ህዝቡ የመዋቅሩ ሰለባ እንዳይሆን የማጋለጥ ሥራ ያከናውናል”  - መድረክ “ተቃዋሚዎችም እንደ ኢህአዴግ የፈለጉትን አደረጃጀት መፍጠር ይችላሉ”  - መኢአብ “ኢህአዴግ አፋኝ ሚሊሻ አድርጎ ያዘጋጃቸው ናቸው” - ኢዴፓ “አደረጃጀቱን ለምርጫ ይጠቀማል የተባለው የሃሰት ውንጀላ ነው”  - ኢህአዴግ ምንጭ፦ www.addisadmassnews.com መንግስት 1 ለ 5 የተሰኘውን አደረጃጀት ለፈጣን ልማታዊ እድገት እየተጠቀመበት እንደሆነ ይናገራል፡፡ በገጠር ይሄንኑ አደረጃጀት ለጤና ኤክስቴንሽን ሠራተኞች ተጠቅሞበት ባስገኘው ውጤት፣ ከኢትዮጵያ አልፎ ለአፍሪካ አገራት ምሳሌ ለመሆን መብቃቱንም በኩራት ይጠቅሳል፡፡ ተቃዋሚዎች በበኩላቸው፤ አደረጃጀቱ ፖለቲካዊ ግብን ያነገበ የስለላ መዋቅር ነው፣ የገዥው ፓርቲ የምርጫ ማስፈፀሚያና መቆጣጠሪያ መዋቅር ነው ሲሉ ይተቻሉ፡፡  ኢህአዴግ በ1 ለ 5  አደረጃጀት በመላው ሃገሪቱ የልማት እንቅስቃሴዎችን በማፋጠን ረገድ ስኬታማ እየሆንኩ ነው ቢልም ተቃዋሚዎች ግን ለአፈና እየተጠቀመበት ነው ይላሉ፡፡ “ከክልል ክልል፣ ከወረዳ ወረዳ ተዘዋውረን ህዝብን በአላማችን ስር ማሰለፍና ማደራጀት ቸግሮናል፣ አባላቶቻችንና ደጋፊዎቻችን እስራትና ድብደባን ጨምሮ ለብዙ እንግልት እየተዳረጉ ነው፣ እንኳንስ ሰፊ ህዝባዊ መሰረት ያለው አደረጃጀት ልንፈጥር በአንድ ወረዳ ውስጥ እንኳን  ፅ/ቤት መክፈት አቅቶናል፣ ከአዲስ አበባ ህዝብ የማደራጀት ተልዕኮ ተሰጥቷቸው የተሸኙ አመራሮች፣ የወረዳ ሹማምንት ሰለባ ይሆናሉ” የሚሉት ተቃዋሚ ፓርቲዎች፤ ገበሬው 1 ለ 5 ካልተጠረነፈ፣ ማዳበሪያና ምርጥ ዘር የመሳሰሉ የግብርና ግብአቶችን ማግኘት

Fair trade not helping workers who pick crops, study shows

Image
Fair trade monitoring process questioned in wake of findings in Ethiopia and Uganda A new study of plantations in Ethiopia and Uganda found casual workers who pick the coffee may be paid less on Fair Trade-dominated farms than on larger plantations or areas without a Fair Trade designation. (Kent Gilbert/Associated Press) The Fair Trade certification movement asks consumers of coffee, tea, sugar and chocolate to pay a little more for the product to help the people who grow and pick the coffee to a better life. But a new report by an economist from the University of London finds the Fair Trade certification movement may not be living up to its billing. THE CURRENT: How fair is fair trade?   Fair trade products hold their own during recession Christopher Cramer co-author of  Fairtrade, Employment and Poverty Reduction in Ethiopia and Uganda  studied 12 sites in Ethiopia in Uganda, comparing the wages of hired labour in areas with large plantations, areas with small f

መድረክ ሕይወታቸው ላለፈና ንብረታቸው ለወደመባቸው ዜጎች መንግሥት ካሳ እንዲከፍል ጠየቀ

Image
ምንጭ፦ www.ethiopianreporter.com   የአዲስ አበባና በዙሪያዋ የሚገኙ የኦሮሚያ ልዩ ዞን ከተሞችን ተጠቃሚ የሚያደርገውን  የተቀናጀ የጋራ ማስተር ፕላን መሠራትን አስመልክቶ፣ በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ የተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች ባደረጉት ሰላማዊ ሠልፍ ላይ በተፈጠረ ግጭት ሕይወታቸው ላለፈ ቤተሰቦችና ንብረታቸው ለወደመባቸው ባለሀብቶች፣ መንግሥት ካሳ መክፈል እንዳለበት የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) ጠየቀ፡፡  መድረክ ‹‹ለሰላማዊ ተቃውሞ ጥይት ምላሽ ሊሆን አይገባም›› በሚል መሪ ቃል ግንቦት 16 ቀን 2006 ዓ.ም. መነሻውን ከግንፍሌ ወንዝ ድልድይ አድርጐ በቤልኤር ሆቴል፣ በህንድ ኤምባሲ፣ በአዋሬ አደባባይና በአድዋ ድልድይ በማድረግ በድንበሯ እናቶችና ሕፃናት ሆስፒታል ጀርባ በሚገኘው የካ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስምንት ሜዳ ላይ ባጠናቀቀው ሰላማዊ ሠልፍ ላይ፣ ከማስተር ፕላኑ ጋር በተያያዘ የተለያዩ ሐሳቦችን አቅርቧል፡፡ የመድረክ አባልና የፓርላማ ተመራጭ የነበሩት አቶ ገብሩ ገብረ ማርያም መድረክ ለምን ሰላማዊ ሠልፍ ለማድረግ እንደተገደደ ሲናገሩ፣ ‹‹ኢሕአዴግ ራሱ ላወጣው ሕገ መንግሥት ባለመገዛት ኢሕገ መንግሥታዊነቱን አረጋግጧል፡፡ ትግላችን ኢዲሞክራሲያዊ ሒደቶች እንዲታረሙ ነው፡፡ በአገሪቱ በተለይ በኦሮሚያ ክልል የተከሰተው ችግር የዲሞክራሲና የሕገ መንግሥታዊ አስተዳደር እጦት ነው፤›› ብለዋል፡፡  ሕገ መንግሥቱ ሲጣስ ‹‹መብቴ ተጥሷል›› ማለት ሕገ መንግሥታዊ መብት መሆኑን የገለጹት አቶ ገብሩ፣ የአዲስ አበባንና የልዩ ዞኖቹን የጋራ ልማት ትስስር ሽፋን፣ ሕዝብ ያልተወያየበትንና ያልተስማማበትን ለመተግበር መነሳት ኢሕገ መንግሥታዊ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ሕዝቡና የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ያነሱ